ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
126

የአማካሪዎች የፍላጎት መግለጫ/ Request for Expression of Interest Consultancy service/

የወልዲያ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ በመደበኛ በጀት በ2017 በጀት ዓመት የድዛይንና የEIA ሥራ /short list/ በማድረግ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ የሥራዉ አላማ፡- ለተጠቀሰዉ ሥራ የland fill, የወጭ መብራት ዝርጋታ፣ ግሪን ኤሪያ፣ የወልድያ ከተማ የሚገልጽ ሎጎ እና ዘመናዊ ቄራ ድዛይንና የማማከር ሥራ በሎት ለሁሉም ሥራዎች የEIA/አካባቢና ማህበራዊ ተጽኖ/ ሥራ መስራት ይሆናል፡፡ ዝርዝር ሥራዎች በቢጋር/TOR/ ላይ በመወዳደሪያ ሃሳብ ማቅረቢያ /Request for Proposal/ ሰነድ ዉስጥ ተዘርዝሮ ቅድመ  መረጣውን ለሚያልፍ ተወዳዳሪዎች /short list firms/ ይሰጣል፡፡ በመሆኑም ከላይ በተጠቀሰው ሥራ ላይ ለመወዳድር ፍላጎትና በቂ ልምድ ያላቸው  ቅደመ መረጣ ለማድረግ የሚያስፈለጉ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን ማስረጃዎች በማቅረብ ፍላጎታችሁን እንድትገልጹ ይጋብዛል፡፡

  1. በዘረፉ በዘመኑ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡትን እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡
  2. ከዚህ በፊት በዲዛይን ሥራና ማማከር ሥራ በቂ ልምድ ያላቸው ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. ለማማክር ሥራ ሊያሰማራቸው የሚችሉ ቁልፍ ባለሙያዎች ያሉት እና የትምህረት ዝግጅትና የሥራ ልምዳቸው ማስረጃ የሚያቀርቡ፡፡
  4. ሌሎች ለቅድመ መረጣ /ውድድር ላይ ያግዛሉ የሚባሉ የድርጅቱን የመፈፀም አቅም ደረጃና መስሪያ ቁሳቁስ የሚያስረዱ ማስረጃዎችን የሚያቀርቡ፡፡
  5. ሥራውን ለመስራት ፍላጎት ያላቸው አማካሪ ድርጅት ከላይ የተዘረዘሩትን ማስረጃዎችን በየ ገጹ የድርጅቱን ማህተምና ሙሉ አድራሻ በመግለፅ ከማመልከቻ ጋር ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  6. የድርጅቱ ህጋዊ ማህተም ያልተደረገበትና ማመልከቻ የሌለው የፍላጎት መግለጫ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
  7. የአካባቢ ማህበራዊ ተፅዕኖ ሰነድ በክልሉ መመሪያ ቁጥር 001/2010 መሰረት ፈቃድ ላለው አካል /sub contractor/ ሰጥቶ ማሰራትና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡ ሲሆን ይህ የፍላጎት መግለጫ /Expression of Interest/ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከ09/03/2017 እስከ 24/03/2017 ባለው ተካታታይ ቀናቶች በወልድያ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ግዥና/ፋ/ ንብ/አስተዳደር የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 13 ተገኝተው ማስረከብ ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታውም የቅድመ መረጣ ሥራ ፋላጎት የመጨረሻ ቀን 24/03/2017 4፡00 ቅድመ መረጣ ማድረግ ይጀምራል፡፡ ቅድመ መረጣው እንደተጠናቀቀ ላለፉትና ለተመረጡት /short list firms/ የመወዳደሪያ ሀሳብ መጠየቂያ ሰነድ ይሰጣቸዋል፡፡
  8. የፍላጎት መግለጫ ሰነዱ በድርጅቱ ህጋዊ ማህተም የተረጋገጠ መሆን አለበት ሥርዝ ድልዝ ወይም አሻሚ የሆነ ፅሁፍ መኖር የለበትም፡፡ መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ የፍላጎት መግለጫ ማስታወቂያውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብት አለው፡፡
  9. ተጨማሪ ማብራያ ካስፈለገ ከሰኞ እስከ አርብ ባሉት የሥራ ቀናት ዘወትር በሥራ ስዓትበአካል በመገኘት ወይም በሥልክ ቁጥር 033 331 03 22 /033 331 18 61/  033 333 13 31 መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የወልድያ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here