በማከላዊ ጎንደር በታች አርማጭሆ ወረዳ የሳንጃ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በ2018 በጀት አመት ከ01/11/2018 እስከ ሰኔ 30/2019 ድረስ ለሆስፒታሉ ሰራተኞች ሰርቪስ አገልግሎት የሚውል መኪና በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በዓ/ህግ ውል ወስዶ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- መኪናው የሚፈልጋቸውን ወጭዎች ከናፍጣ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ባለንብረቱ (ባለሃብቱ) የሚሸፍን ነው፡፡
- ከሀምሌ 01/2018 እስከ ሰኔ 30 /2019 ዓ/ም ድረስ ውል ሊወስድ የሚችል፡፡
- የመኪና ሊብሪ ያላቸው ሆኖ ሆስፒታሉ ዝቅተኛ ዋጋ በሞላ ተወዳዳሪ አሸናፊዉን የሚለይ ይሆናል፡፡
- የመኪናው የምርት ዘመን ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ የሆነ እና መኪናው 45 ወንበር እና ከዚያ በላይ የሆነ፡፡
- በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-6 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከማጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል የሳንጃ የመጀመሪያ ደርጃ ሆስፒታል ግ/ፋ/ን/አስ/ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፡፡ ጨረታው ከወጣበት ከየካቲት 02/2018 ዓ/ም እስከ የካቲት 16/2018 ዓ/ም ለተከታታይ 15 ቀናት ይቆያል፡፡
- የጨረታው ሳጥን የሚታሸገው የካቲት 17/2018 3፡30 ይሆናል፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው ሁሉም ተጫራቾች ወይም ወኪላቸው ባሉበት የሳንጃ የመ/ደ/ሆስፒታል አዳራሽ በ- የካቲት 02/2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ይሆናል፡፡ ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸዉ ባይኖርም የሚከፈት ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ብር አንድ በመቶ ጠቅላላ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ኦርጀናልና ኮፒውን ለየብቻ በመለየት በጥንቃቄ በታሸገ ፓስታ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ማስገባት ይኖርበታል፡፡
- ከጨረታ ሰነዱ ላይ ከተጠቀሰው የዋጋ መሙያ ፎርም በስተቀር በማሳሰቢያ የሚሞሉ የዋጋና ሌሎች አላስፈላጊ መረጃዎችን የማንቀበል መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- አሸናፊ ድርጀት የውል ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን 10 በመቶ ማስያዝ የሚችል፡፡
- ሆስፒታሉ የሚገኛዉ ሰርቢስ ከሚጀምርበት ቦታ ጀምሮ 3 ኪ/ሜ እርቀት አለዉ በመሆኑም ጠዋት 1፡50 ወደ ስራ ለምሳ 6፡30 ከምሳ መልስ 8፡20 እንዲሁም ማታ ወደ ቤት 11፡30 በድምሩ 4 /አራት/ ዙር እና እሁድና ቅዳሜ 2፡30 ወደ ቢሮ 11፡30 ወደ ቤት በድምሩ ሁለት ዙር ማመላለስ አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለዋስትና የሚያዘው ሲፒኦ በቁጥርና በፊደል የተጻፈው የተለያየ ከሆነ ተቀባይነት የለውም፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 18 19 85 88 /09 39 24 50 07 /058 273 03 94 ደዉለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የሳንጃ የመጀመሪያ ደርጃ ሆስፒታል

