የዋድላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለዋድላ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት አገልግሎት የሚሆን በሰቆጣ ቃል ኪዳን ድርጅት የአምባ ጋሸና 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የታድላ መንደር ቅድመ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የቁርቁር 1ኛ ደረጃ ት/ቤት የመጸዳጃ ቤት ግንባታ ስራን ለማሰራት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተወዳዳሪዎች ድርጅቶች ሁሉ ከዚህ በታች የተጠየቁትን መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባችኋል፡፡
- ህጋዊና በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የተሰጣቸው ለዚህም ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚሞሉት ዋጋ ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) እና በላይ ከሆነ ተጫራቾች የቫት ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ለጨረታዉ የሚቀርቡ ተወዳዳሪዎች ደረጃ 8 እና ከዚያ በላይ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በወጣ በ22ኛው ቀን ይከፈታል፡፡ ባይገኙም ግን በግን/አስ/ቡድን ቢሮ በግልጽ የሚከፈት ሲሆን ተጫራቾች በጨረታ ሂደቱ በተላለፈው ውሳኔ ተገዥ ይሆናሉ፡፡ ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይከፈታል፡፡
- ማንኛውም ተጫራቾች በሚሞላው ዋጋ ላይ ሥርዝ ድልዝ ወይም አሻሚ የሆነ ዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ እና ያልተሟላ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ ስምና ፊርማቸውን የድርጅቱን ማህተም በማድረግ የገዙትን ሙሉ ሰነድ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ጨረታ ማስከበሪያ 2 በመቶ በሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማሲያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- አሸናፊው ድርጅት አሸናፊነቱ ከተገለጸ በኋላ የውል ማስከበሪያ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ በተረጋገጠና በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በሲፒኦ በጥሬ ገንዘብ ማሲያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ሲሆን ጨረታውን በመሰረዙ ተጫራቾች በጨረታው ላወጡት ውጭ መ/ቤቱ ሃላፊነቱን አይወስድም፡፡
- ስለጨረታው ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 09 20 01 39 41 ወይም 09 80 51 37 26 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የዋድላ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

