ግልጽ የጨረታ ማስታዎቂያ

0
16

የወረታ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ለሴክተር መ/ቤቶች ለ2018 በጀት ዓመት ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ፣ ሎት 2 ኤሌክትሮኒክስ፣ ሎት 3 የጽዳት እቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ማንኛውም ተጫራቾች ሁሉ መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸዉ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸዉ፡፡
  4. የግዥው መጠን ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ወይም (ቫት) ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ ለሚወዳደሩበት ለእያንዳንዱ በመክፈል ወረታ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 21 መግዛት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ወይም (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳዳሩበት የዕቃ ጠቅላላ ዋጋ 2 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዛ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና እንዲሁም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸዉ፡፡
  7. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱንና ንግድ ፈቃዱ በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በተለያየ ፖስታ በጥንቃቄ በማሸግ በወረታ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ወይም ቢሮ ቁጥር 22 በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ዘወትር በሥራ ስዓት ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት ውስጥ መግዛትና ማስገባት ይችላሉ፡፡
  8. ጨረታው በጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን በ3፡30 ታሽጎ በዚያው ቀን ከረፋዱ 4፡00 ይከፈታል፡፡
  9. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀናት በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ይከፈታል፡፡
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  12. ጨረታው በወጣው ማስታወቂያ መሠረት 20 በመቶ ሊቀንስም ሊጨምርም ይችላል፡፡
  13. አሸናፊው ድርጅት እቃውን ወረታ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ድረስ ማቅረብ አለበት፡፡
  14. ውድድሩ በጥቅል ነው፡፡
  15. ጨረታው በግዥ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 1/2003 መመሪያ መሰረት የሚፈጸም ይሆናል፡፡
  16. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 22 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 446 13 45 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

ማሳሰቢያ፡- የሚሞሉት ነጠላ ዋጋ ሥርዝ ድልዝ ካለው ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡

የወረታ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here