ግልጽ የጨረታ ማስታዎቂያ

0
36

የደብረ ማርቆስ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በ2018 በጀት ዓመት ለሆስፒታሉ አገልግሎት የሚዉል የተለያዩ ህትመቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሳተም ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-

  1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው እና የንግድ ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  2. በዚህ ጨረታ ከ200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ የሚሳተፉ ተጫራቾች (ቫት) ተመዝጋቢ መሆን አለባቸዉ፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ጨረታ ማስከበሪያ ብር 3,000 /ሶስት ሺህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ኦርጅናሉን ወይም በጥሬ ገንዘብ የተያዘ ከሆነ የደረሰኞችን ፎቶ ኮፒ ከፋይናንስ ወይም ከዋጋ ማቅረቢያ ፖስታ ውስጥ አስገብቶ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  4. ጨረታው 15 ቀን በጋዜጣ ወጥቶ ቆይቶ በ16ኛው ቀን በ8፡00 ታሽጎ 8፡30 ይከፈታል፡፡
  5. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  6. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሆስፒታሉ አዳራሽ ይካሄዳል፡፡
  7. የተጫራቾች አለመገኘት የጨረታውን መከፈት አያግደውም፡፡
  8. የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ከግ/ፋ/ን/አ/ደ/የስ/ቡድን ቢሮ ጥር 4 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  9. ሆስፒታሉ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. የጨረታ ዋጋ ፀንቶ የሚቆይበት ጨረታዉ ከተከፈተበት ቀን አንስቶ የሚቆጠር ዝቅተኛ ቀን ከ40 ቀናት ፀንቶ ይቆያል፡፡
  11. የጨረታ መዝጊያ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለዉጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታዉ ራሳቸዉን ማግለል አይችሉም፡፡
  12. ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ከግ/ፋ/ን/አ/ደ/የስ/ቡድን በአካል በመገኘት በስልክ ቁጥር 058 771 22 46 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የደብረ ማርቆስ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here