ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

0
17

በደቡብ ጎንደር ዞን ለደብረታቦር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አገልግሎት  የሚውል የተለያዩ የህንፃ እድሳት ለማስጠገን  ፈቃዳቸው ከደረጃ 1-4 ያሉ ተቋራጭ እና ልዩ የሥራ ተቋራጭ እንዲሁም  በ2017 ዓ/ም ግንባታ ገንብተው መልካም ሥራ አፈፃፀም ካላቸው ተቋራጮች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በዝቅተኛ ዋጋ ከሞሉ ተወዳዳሪዎች ማሰራትና ማስጠገን  ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ማስረጃ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፍያ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትን እና የሚፈለግባቸውን ማስረጃዎች ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ጋር በማቅረብ ኮፒውን ከተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ጋር በማያያዝ ከኮሌጁ ግዥ ባለሙያ ቢሮ  ፊት ለፊት ከሚገኝው ሳጥን ማስገባት ይኖረባቸዋል፡፡
  5. ተጫራቾች ጠቅላላ ድምር ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ወይም (ቫት) ተመዝጋቢ መሆን አለባቸዉ፡፡
  6. ተጫራቾች የሚስራውን የስራ አይነት (ስፔስፊኬሽኑን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ኮሌጁ ቫት ከብር 20,000 (ሃያ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ  እና ዊዝሆልዲንግ ታክስ ብር 10,000 (አስር ሺህ ብር) በላይ ከሆነ ኮሌጁ ግብር ሰብሳቢ ስለሆነ ቀንሶ ያስቀራል፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ለመግዛት የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) ከኮለጁ ገንዘብ ያዥ ቢሮ ቁጥር 7 መክፈል የተዘጋጀውን ሰነድ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  9. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋሰትና (ቢድ ቦንድ) ጨረታው ከመከፈቱ በፊት (በሲፒኦ) በጥሬ ገንዘብ ከሚሞላው ጠቅላላ ዋጋ ብር አንድ በመቶ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማስያዝ አለባቸው፡፡
  10. ማንኛውም ተጫራች የሚጫረትበትን ዋጋ በተዘጋጀው ሰነድ ላይ በመሙላት በጥንቃቄ በታሸገ ፓስታ ላይ ስሙን እና አድራሸውን በመፃፍ ደብረ ታቦር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በግዥ ቢሮ ቁጥር 1 በተዘጋጀዉ ሳጥን ጨረታዉ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21 ተከታታይ ቀናት በጋዜጣ ከወጣበት በሥራ ቀናት ማስገባት ይችላሉ፡፡
  11. ጨረታዉ የሚከፈትበት በ22ኛው ቀን በ4፡00 ታሽጎ በ4፡15 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ ቢገኙም ባይገኙም ጨረታዉ ይከፈታል እለቱ ቅዳሜ እና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  12. ተጫራቾች ዋጋ ሲሞሉ ሥርዝ ድልዝ ካለው ከውድድር ውጭ ይሆናሉ፡፡ ፓራፍ (ልዩ ፊርማ ቢያደርጉም) ከውድድር ውጭ ይሆናሉ፡፡
  13. ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  14. ተጫራቹ የሚያቀርበዉን ደረሰኝ በራሱ ስም የታተመና ተከታታይ የደረሰኝ ቁጥር ያለዉ መሆን አለበት
  15. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 441 05 99 በመደወል ወይም ከኮሌጁ የግዥ ባለሙያ ቢሮ ቁጥር 1 በአካል በመገኘት መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

ደብረታቦር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here