ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

0
110

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የባሕር ዳር ከተማ አስ/ከተማ እና መሰረተ ልማት መምሪያ በ2016 በጀት ዓመቱ የፓምፕ ግዥ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር እንደምትችሉ እንገልጻለን፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. ግብር ከፋይ መለያ (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የግዥ መጠኑ 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው፡፡
  4. ተጫራቾች ጨረታውን ለመሳተፍ ከተ.ቁ 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ኮፒ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. የተጫራቾች የጨረታ ማስከሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ብር ወይም የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ 198,000.00 (አንድ መቶ ዘጠና ስምት ሺህ ብር) ብቻ በባንክ በተረጋገጠ ክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ አለባቸው፡፡
  6. የጨረታ አሸናፊ የሚለየው በነጠላ ዋጋ ነው፡፡
  7. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሱቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ማለትም ኦርጅናል እና ኮፒ ተለይቶ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በግዥ /ንብ/አስ/ ቡድን ወይም ቢሮ ቁጥር 205 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ጨረታ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ከ2፡30 እስከ 15ኛው ቀን 11፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ጨረታ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ/ን/አስ ቡድን ክፍል በቢሮ ቁጥር 205 በ15ኛው ቀን በ11፡00 ታሽጎ በ16ኛው ቀን በ3፡30 ይከፈታል፡፡ ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ከሥራ ቀናት ውጭ ከሆነ ወደሚቀጥለው የሥራ ቀን ይዛወራል፡፡
  9. ጨረታው ሁለት የግምገማ ሂደቶች ይኖሩታል፡፡ የመጀመሪያው ሂደት /ደረጃ የቴክኒካል ሰነዶች ግምገማ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ቴክኒካል ግምገማውን ካለፉት ተጫራቾች ውስጥ የአማራ ብሔራዊ መንግስት ገንዘብ ቢሮ በቁጥር አብክመ ገ/ቢ/ኮቢ01/02 በቀን 15/09/2014 ዓ.ም በተሻሻለው መመሪያ መሰረት የጨረታ ዋጋ ያቀረበውን ተጫራች መምረጥ ይሆናል፡፡ ለበለጠ መረጃ ይህን መመሪያ በደንብ ያንብቡት፡፡
  10. የፓምፕ ግዥ አሸናፊ ለምትሆኑ ተጫራቾች ግዥው የሚፈጸመው መሥሪያ ቤቱ /ግዥ ፈፃሚው በሚያቀርበው ናሙና ላይ የተመሰረተ ይሆናል፡፡
  11. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 205 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በመላክ ወይም በስልክ ቁጥር 058 320 18 78 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
  12. የጨረታ ሰነድ መግዛት የሚፈልጉ ማንኛውም ሕጋዊ ተጫራቾች የማይመለስ 1,500.00 (አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
  13. የፓምፕ ግዥ ሥራ ወጭዎችን የሚሽፍነው አሸናፊ ተጫራች ይሆናል፡፡
  14. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በክፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

የባሕር ዳር ከተማ አስ/ ከተማ እና መሰረተ ልማት መምሪያ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here