የፍ/ሰላም ከተማ አስተዳደር ወጀት ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ለመንገድ ሥራ አገልግሎት የሚውል ስሚንቶ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፣
- በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው፡፡
- የግዥው መጠን 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስራጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገዙ የዕቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
- የተሞላው ዋጋ ማንኛውንም ግብር ወይም ታክስ ያካተተ መሆን አለበት፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያና ዋስትና ለሚወዳድሩበት ብር ወይም ዕቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ሲ.ፒ.ኦ ወይም ጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የዋጋ መሙያ ሰነዳቸው ላይ ማህተምና ፊርማ በማድረግ በፖስታ በማሸግ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት በአስር ተከታታይ የሥራ ቀናት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ደጋፊ የሥራ ሂደት ጨረታው ከወጣበት ቀን ለአስር ተከታታይ የሥራ ቀናት በአየር ላይ ይውልና በአስራ አንደኛው ቀን በ4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል፣ ባይገኙም ጨረታውን ለመክፈት አያስተጓጉልም፡፡
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 09 13 75 77 87 /058 775 22 54 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ጨረታውን ካሸነፉ የተጫረቱትን የግንባታ ቁሳቁስ አጓጉዘው ፍ/ሰላም ከተማ መሥሪያ ቤቱ ያዘጋጀው ቦታ ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታውን ካሸነፉ የተጫረቱትን የግንባታ ቁሳቁስ አጓጉዘው በፍጥነት ማቅረብ መቻል አለባቸው፡፡
- ከላይ ስለ ጨረታው ያልተገለጹ ነገሮች ቢኖሩ በ2003 የግዥ አፈፃፀም መመሪያ መሰረት ተፈፃሚ ይሆናሉ፡፡
ወጀት ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ