ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

0
117

የደብረ ማርቆስ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በ2017 በጀት ዓመት ለሆስፒታሉ የሠራተኞች የሰርቪስ አገልግሎት የሚሰጥ 60 እና ከዚያ በላይ ወንበር ያለው 1ኛ ደረጃ አውቶቢስ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-

  1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ እና የንግድ ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡
  2. ግዥው ከ200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ጨረታ ማስከበሪያ 3,000.00 /ሦስት ሺህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ኦርጅናሉን ወይም በጥሬ ገንዘብ የተያዘ ከሆነ የደረሰኞችን ፎቶ ኮፒ ከፋይናንስ ወይም ከዋጋ ማቅረቢያ ፖስታ ውስጥ አስገብቶ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  4. ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 15 ቀን በአየር ላይ ቆይቶ በ16 ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ 8፡00 ይከፈታል፡፡
  5. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  6. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሆስፒታሉ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይካሄዳል፡፡
  7. የተጫራቾች አለመገኘት የጨረታውን መከፈት አያግደውም፡፡
  8. የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ከግ/ፋ/ን/አ/ደ/የስ/ሂደት ቢሮ ቁጥር 4 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  9. ሆስፒታሉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. የጨረታ ዋጋው ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተበት ቀን አንስቶ የሚቆጠር ዝቅተኛ ቀን 40 ቀናት ይሆናል፡፡
  11. የጨረታ መዝጊያ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
  12. ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ከግ/ፋ/ን/አ/ደ/የስ/ሂደት በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 771 22 46 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የደብረ ማርቆስ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here