ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

0
121

በደቡብ ወሎ ዞን የተሁለደሬ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በመደበኛ በጀት ለወረዳው መኪኖች አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1. የመኪና እቃ፣ ሎት 2. የመኪና ጎማ ከነካለማደሪያው በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  1. ሕጋዊና የታደሰ ንግድ ፈቃድና ቲን ያላቸው፡፡
  2. የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
  3. ከተ.ቁ 1-2 የተዘረዘሩትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውንና ተፈላጊ መረጃዎችን የዋጋ ማቅረቢያ ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ በማለት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  4. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያ በታሸገ ኢንቨሎፕ የመወዳደሪያ ዋጋቸውን ኦርጅናልና ኮፒ በማለት የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ በመሆኑ መሥሪያ ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
  5. ጨረታው በ16ኛው ቀን ከቀኑ 4፡00 ታሽጎ በዚሁ ቀን 4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ይከፈታል፡፡
  6. የጨረታ መክፈቻው ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ ጨረታው በቀጣይ የሥራ ቀን የመክፈቻ ሰዓቱን ጠብቆ ይከፈታል፡፡
  7. ተጫራቾች የእቃ አገልግሎት ዝርዝር ማቅረቢያ ሰንጠረዥ ውስጥ የአንዱ ዋጋና ጠቅላላ ዋጋውን እንዲሁም ቀን፣ ፊርማና የድርጅቱን ማህተም ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  8. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ጠቅላላ ዋጋ ታክስን የሚያካትት ወይም የማያካትት መሆኑን መግለጽ አለባቸው፡፡
  9. አሸናፊው የሚለየው በሎት ድምር ዋጋ ነው፤ በሰነዱ የተዘረዘሩትን እቃዎች ዋጋ በሙሉ ያልሞላ ተጫራች ከጨረታው ውጭ ይሆናል፤ አሸናፊ ሆኖ የተመረጠው ተጫራች መሥሪያ ቤቱ በጠየቀው ስፔስፊኬሽን መሰረት የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡
  10. ተጫራቾች የሞሉት ዋጋ ከወቅቱ የገበያ ዋጋ ጋር ሲነፃፀር የተጋነነ ከሆነ ጨረታው ውድቅ ይሆናል፡፡
  11. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
  13. ጨረታውን ለማዛባት የሞከረ ተጫራች ከጨረታው ውጭ ሆኖ ወደፊትም በመንግሥት ጨረታ እንዳይሳተፉ ይደረጋል፡፡
  14. አሸናፊው የተጫረተውን የመኪና እቃና ጎማ ማሸነፉ እንደተገለፀ ውል የመውሰድና ንብረቱን በራሱ በማጓጓዝ ግዥ ፈጻሚ ንብረት ክፍል ድረስ የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡
  15. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 033 222 00 12 መደወል ይችላሉ፡፡

የተሁለደሬ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here