ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

0
122

የደብረ ማርቆስ አጠቃላይ ስፔሻላዝድ ሆስፒታል በ2017 በጀት ዓመት ለሆስፒታል አገልግሎት የሚውል ሴኪዩሪቲ ካሜራ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-

  1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው እና የንግድ ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን ያላቸው፡፡
  2. በዚህ ጨረታ የሚሳተፉ ተጫራቾች ቫት ተመዝጋቢ ብቻ መሆን አለባቸው፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት የጨረታ ማስከበሪያ 3,000.00 /ሦስት ሺህ / ብር ብቻ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ኦርጅናሉን ወይም በጥሬ ገንዘብ የተያዘ ከሆነ የደረሰኞችን ፎቶ ኮፒ ከፋይናንስ ወይም ከዋጋ ማቅረቢያ ፖስታ ውስጥ አስገብቶ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  4. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአየር ላይ ለ15 ቀን ቆይቶ በ16 ተኛው ቀን ይከፈታል፡፡
  5. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  6. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሆስፒታሉ የስብሰባ አዳራሽ ይካሄዳል፡፡
  7. የተጫራቾች አለመገኘት የጨረታውን መከፈት አያግደውም፡፡
  8. የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ከግ/ፋ/ን/አ/ደ/የስ/ሂደት ቢሮ ቁጥር 4 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  9. ሆስፒታሉ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. የጨረታ ዋጋ ፀንቶ የሚቆይበት ጨረታው ከተከፈተበት ቀን አንስቶ የሚቆጠር ዝቅተኛ ቀን ከ40 ቀናት ፀንቶ ይቆያል፡፡
  11. የጨረታ መዝጊያ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለዉጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታዉ ራሳቸዉን ማግለል አይችሉም፡፡
  12. ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ከግ/ፋ/ን/አ/ደ/የስ/ሂደት በአካል በመገኘት/ በስልክ ቁጥር 058 771 22 46 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

 

የደብረ ማርቆስ አጠቃላይ ስፔሻላዝድ ሆስፒታል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here