ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

0
94

የዳግማዊ ምኒልክ ጤና ጣቢያ የላብራቶሪ ጣራ ክዳን፣ የህሙማን መቆያ እና ሌሎች ስራዎችንም በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ከዚህ  በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

  1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፡፡
  2. የዘመኑ ግብር የከፈሉ ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸዉ እና የታተመ ተከታታይ ደረስኝ ቁጥር ያላቸዉ፡፡
  4. የግዥው መጠን ከ200‚000(ሁለት መቶ ሽህ ብር) በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፍኬት ያላቸው፡፡
  5. የግዥው መጠን ከ 10‚000(አስር ሽህ) በላይ ከሆነ 2በመቶ ዊዝ ሆልዲንግ ታክስ ይቆረጥባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ አንድ በመቶ የመጫረቻ ዋጋውን ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር በፖስታ አሽጎ በማስገባት ከጨረታ ሳጥኑ ገቢ ማድረግ አለባቸው፡፡
  7. ተወዳዳሪዎች ደረጃ 7 እና ከዛ በላይ መሆን አለባቸው፡፡
  8. አርቲሜቲክ ቼክ ከ2.5 በላይ ከሆነ ከውድድር ውጭ ይሆናሉ፡፡
  9. ሰነዱ ስርዝ ድልዝ ካለው ከውድድር ውጭ ይሆናል፡፡
  10. የጨረታ ሰነዱን ቢሮ ቁጥር 9 ድረስ በመምጣት በ500 (አምስት መቶ )ብር በመግዛት መውሰድ ትችላላችሁ፡፡
  11. የመጫረቻ ሰነዱ በፖስታ ታሽጎ መቅረብ አለበት፡፡
  12. ለመጫረት የሚቀርቡ ማንኛውም ማስረጃዎች ግልፅ፣ በደንብ የሚታይ እና የሚነበብ መሆን አለበት፡፡
  13. ማንኛውም ተጫራች በምታቀርቡት የመወዳደሪያ ሀሳብ ስማችሁን ፣ ስልክ ቁጥር እና የድርጅቱ ማህተም ሊኖር ይገባል፡፡
  14. ጨረታው አየር ላይ የሚውልበት ቀን ከ 29/07/2017ዓ.ም ተከታታይ 15 ቀን ሲሆን ፤ጨረታው የሚያበቃው በ14/08/2017 10፡30 ታሽጎ በ15/08/2017 3፡30 ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  15. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀነዉ ፡፡

የዳግማዊ ምኒልክ ጤና ጣቢያ

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here