ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

0
65

በአብክመ ጤና ጥበቃ ቢሮ የአዲስ አለም ሆስፒታል ለአገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ 3 አይነት ግዥዎችን ሎት1. የፅዳት አውት ሶርስ፣ ሎት2. የምግብ አቅርቦት አውት ሶርስ ፣ሎት3. የጥበቃ አውት ሶርስ በግልፅ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን ያላቸው፡፡
  3. የግብር የከፈሉ ስለመሆናቸው የክሊራንስ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. የፅዳት አውት ሶርስ እና የጥበቃ አውት ሶርስ ከሁለት የመንግት መ/ቤት ወይም ህጋዊ የግል ድርጅት ተቋማት የአንድ አንድ አመት የስራ ልምድ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  6. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-5 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ሰነድ ብር 300 ብር በመክፈል

ከግ/ፋ/ንብ/አስ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 05 ማግኘት ይችላሉ፡፡

  1. በሎት የወጡትን 3ቱንም አይነትና ዝርዝር መግለጫ ወይም እስፔስፊኬሽን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  2. ዝርዝር መግለጫውን ከጨረታ ሰነድ ማግኘት ይቻላል፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስረከቢያ /ቢድ ቦንድ / ለሚወዳደሩ ጠቅላላ ዋጋ 2በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሰፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  4. የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከታተመበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ቆይቶ በ16ኛው ቀን 3፡00 ተዘግቶ በዚያው ቀን ከቀኑ 4፡00  ይከፈታል፡፡
  5. አሸናፊው ማሸነፋ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ለ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን አስር በመቶ የውል ማስያዣ ያስይዛል፡፡
  6. ማንኛውም ተጫራች ሀሳቡን በታሸገ ፖስታ በአዲስ አለም ሆስፒታል ግዥ/ፋይ/ንብ/አስ/ ቡድን በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት አለበት፡፡
  7. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  8. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለ ጨረታው መረጃ ቢሮ ቁጥር 05 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 218 10 34 ደውለው ማግኘት ይችላሉ፡፡

 

የአዲስ አለም ሆስፒታል

ባህርዳር

 

 

 

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here