ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

0
148

የምዕራብ ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ ለግብአት አቅርቦትና ስርጭት ገጠር ፋ/የሥራ ቡድን ለመስኖ አት/ፍራ/ውሃ አጠቃቀም ቡድን አገልግሎት የሚውሉ የአቡካዶ እና ማንጎ ዘር በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ያሳውቃል።

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው::
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው::
  3. የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ እና ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ::
  4. የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ::
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተ.ቁ 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
  6. የሚገዙ የዕቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል::
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የጠቅላላ ዋጋውን አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲ.ፒ.ኦ) ማስያዝ አለባቸው::
  8. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን  በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በግብርና መምሪያው የግብአት አቅርቦት እና ስርጭት ገጠ/ፋይ የሥራ ቡድን ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት  ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት  ቀን ጀምሮ እስከ 16 ኛዉ ቀን 4፡00  ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል:: ለዚህ ጨረታ መወዳደሪያ ሰነድ  የዕቃዎቹ ዝርዝር መግለጫ(spasfication)፣በዘርፋ እና ዘመኑ  የታደሰ  የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን)፣ የማቅረቢያ ቦታ፣ የማቅረቢያ ጊዜ፣ ዋጋው ፀንቶ የሚቆይበት  ቀን ነው::
  9. በጨረታው ለመሣተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ብር 100.00 /አንድ መቶ/ ብር በመክፈል ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛዉ ቀን ድረስ መሥሪያ ቤቱ ወይም ጽ/ቤት በመቅረብ ዘወትር በሥራ ሰዓት መውሰድ ይችላሉ::
  10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግብርና መምሪያው የግብአት አቅርቦት እና ስርጭት የሥራ ቡድን ቢሮ በ16 ኛዉ ቀን 4፡30  ይከፈታል:: በ16ኛው ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን የሚከፈት ይሆናል::
  11. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
  12. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ድረስ በአካል ወይም በፋክስ ቁጥር 058 775 08 81 በመላክ  በስልክ ቁጥር 058 775 08 71 በመደወል ማግኘት ይችላሉ::
የምዕ/ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here