ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

0
199

የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኤሌክትሮኒክስ እቃ በግልጽ  ጨረታ መግዛት ይፈልጋል::ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች  ማስታወቂያው በጋዜጣ  ከወጣበት ቀን ጀምሮ መስፈርቱን የሚያሟሉ መወዳደር ይችላሉ::

  1. በዘርፉ ሕጋዊ ፍቃድ ያላቸውና የታደሠ ንግድ ፍቃድ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ:: የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፣ /ቲን/ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ ሆነው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉና ለእቃው ቀጥተኛ የሆነ የንግድ ፍቃድ ያላቸው መሆን አለባቸው::
  2. ለማንኛውም ተጫራች ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 የሥራ ቀናት ውስጥ ዘወትር በሥራ ሰዓት ማለትም ቅዳሜ ግማሽ ቀን ጨምሮ በመምጣት ሠነድ መውሰድ ይችላሉ::
  3. ተጫራቾች በተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ በኦርጅናል የማወዳደሪያ ዋጋ በመሙላት በፖስታ በማሸግ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ከጨረታው መዝጊያ ቀንና ሰዓት በፊት ማስገባት አለባቸው::
  4. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ከ3ዐ/07/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት የጨረታ ሠነዱን በመግዛት በ10ኛው ቀን ከቀኑ 8፡15 ተዘግቶ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል::
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) በጨረታው ከሚቀርቡ አገልግሎት ከጠቅላላ ዋጋ ላይ ሁለት በመቶ በባንክ በተመሠከረለት ቼክ ወይም ሲ.ፒ.ኦ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል:: ማንኛውም ዋጋ የሚሞላውና ክፍያ የሚፈፀመው በኢትዮጵያ ብር ብቻ ነው::
  6. በጨረታው የሚሳተፈው ተወካይ ከሆነ ሕጋዊ የሆነ ውክልና ማስረጃ ማቅረብ ይኖርበታል፤ ተጫራቾች በወቅቱ አለመገኘት የጨረታውን ሂደት አያስተጓጉልም::
  7. የጨረታው አሸናፊ የሚሆነው ድርጅት አሸናፊነቱ ተገልጾለት ውል ከወሰደበት ቀን ጀምሮ በ10 ቀናት ውስጥ እቃውን ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት::
  8. በጨረታው መካፈል የሚፈልጉ ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ቢፈልጉ በስልክ ቁጥር 058 218 03 41/058 218 11 94 መጠየቅ ይቻላል::
  9. ተጫራቾች ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎችን ማቅረብ አለባቸው::
  10. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::

 

 የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here