የሐራጅ የጨረታ ማስታወቂያ

0
121

በከሣሽ ይንገስ ጌታሁን ህፃን ቴዎድሮስ አይንዋጋ እና በተከሣሽ ዝይን ደርሰህ ህፃን እየሩሣሌም አይንዋጋ ዳግማዊት አይንዋጋ መካከል ስላለው የአፈፃፀም ክስ ክርክር ጉዳይ በእነ ዝይን ደርሰህ ስም ተመዝግቦ የሚገኘው ካርታ ቁጥር አፄ/ቴ 9800/2015 ክ/ከ/ቀበሌ አዲስ አለም በምስራቅ መንገድ፣ በምዕራብ አዛለች ጌታሁን፣ በሰሜን አዝመራ ዘለቀ እንዲሁም በደቡብ ትልቅሰው አፈረ የሚያዋስነው 56.60 ካሬ ሜትር ቦታ በግምት መነሻ ዋጋ ብር 545,258.71/አምስት መቶ አርባ አምስት ሺህ ሁለት መቶ ሃምሣ ስምንት ብር ከ71/100 ሣንቲም/ ሆኖ ህዳር 13/2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 6፡00 ድረስ በግልጽ ጨረታ ይሸጣል፡፡ በመሆኑም መጫረት የምትፈልጉ ሁሉ ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ በስዓቱና በቦታው በመገኘት ተመዝግባችሁ መጫረት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን የመጨረሻ አሸናፊው ያሸነፈበትን ¼ ኛውን በሞዴል 85 ማስያዝ የሚጠበቅበት መሆኑን ፍ/ቤቱ ያሣውቃል፡፡

የባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here