ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
83

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የምዕራብ በለሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም በጀት አመት ለግብርና ጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል በአውሮፓ ዩኒየን የበጀት ድጋፍ ሎት 1. በሹራ ቀበሌ አነስተኛ መስኖ ጠለፋ፣ ሎት 2.በሹራ ቀበሌ 5 በአፀይተራ ቀበሌ 4 በቃላይ ቀበሌ 1 የእጅ ጉድጓድ የንፁህ መጠጥ ውሃ ግንባታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማስገንባት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም፡-  በጨረታው ለመወዳደር መስፈርቱንም የሚያሟሉ መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. ህጋዊ የሆነ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
  4. ለመስኖ ጠለፋው ደረጃ 5 እና ከዚያ ሲሆን ለንፁህ ውሃ መጠጥ ደረጃ 8 እና ከዚያ በላይ የሆኑ፡፡
  5. ጨረታ ለመስኖ የፋይናሻልና ቴክኒካል ይጠይቃል፡፡
  6. ተጫራቾች ጨረታው ከወጣበት በጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ የጨረታ ሰነዱን ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምዕራብ በለሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ዘወትር በስራ ቀን ቢሮ ቁጥር 13 በመምጣትና ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን አንድ ወጥ በሆነ ሁለት ፖስታ ማለትም ኦርጅናልና ኮፒ በማለት በጉልህ በተፃፈ አድራሻ ምዕራብ በለሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖባቸዋል፡፡
  8. ተጫራቾች ለሚሞሉት ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሆነ ምዕራብ በለሳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 13 ከረዳት ገንዘብ ያዥ ገንዘቡን ገቢ በማድረግ የገቢ ደረሰኙን ከስነድ ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. አሸናፊው አካል ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ የውል ማስከበሪያ በተራ ቁጥር 6 ከተገለፀው ተቋም ማስያዝ አለበት፡፡
  10. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብት የተጠበቀ ነው፡፡
  11. ማንኛውም ተጫራች ዋጋ ሲሞላ ሥርዝ ድልዝ ካለው ከፊት ለፊቱ ልዩ ፊርማውን ማስቀመጥ ይኖርበታል፡፡
  12. ማንኛውም ተጫራች ፖስታው ላይም ሆነ ከጨረታ ሰነዱ ስም ፊርማ፣ ማህተም ስልክ ቁጥር እና ሙሉ አድራሻውን መፃፍ ይኖርባቸዋል፡፡
  13. የውሃ ግንባታው የእጅ ዋጋን እና የማቴሪያልን ጨምሮ ሙሉ ግንባታ ነው፡፡
  14. ይህ ጨረታ በክልሉ የግዥ እና ንብረት አስተዳደር መመሪያ የሚተዳደር ይሆናል፡፡
  15. ጨረታው ለተከታታይ 15 ቀናት በጋዜጣ ወጥቶ ይቆያል፡፡

የምዕራብ በለሳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here