ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
58

በአማራ  ብሔራዊ  ክልላዊ  መንግስት መሬት ቢሮ በፕሮጀክት በመደበኛ  እና በመደበኛ ካፒታል በጀት ለቢሮው አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ፣ የጽዳት እቃዎች፣ የጽ/መሳሪያ እቃዎች፣ የደንብ ልብሰ፣ የመኪና ጎማ ፣የፈርኒቸር፣ የህትመት ሥራ አገልግሎት ግዥ እና የቶታል እስቴሽን (የቅየሳ መሳሪያ እና መለዋወጫ እቃዎች) ግዥ  በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡

  1. በዘርፉ አግባብ ያለው እና የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግዥ መጠኑ ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-2 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል በአብክመ መሬት ቢሮ ቁጥር 18 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  5. የእቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽ) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. አሸናፊ ድርጅት የሚለየው የተጠቀሰውን ዝርዝር መግለጫ ያሟላ ሆኖ በነጠላ ዋጋ ዝቅተኛ ሞልቶ ያቀረበ ነው፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ 2 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በማሰራት ደረሰኙን ከመጫረቻ ሠነዱ ጋር በማያያዝ በታሸገ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  8. ማንኛውም ተጫራች ዋናውን ፋይናንሻል የመጫረቻ ሰነዱ በፖስታ በጥንቃቄ በማሸግ በአብክመ መሬት ቢሮ ቁጥር 18 ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ማለትም ከየካቲት 30/2018 ዓ.ም እስከ መጋቢት 15/2018 ዓ.ም እስከ 3፡00 ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአብክመ መሬት ቢሮ ቁጥር 18 መጋቢት 15/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 3፡00 ታሸጐ በዚሁ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ይከፈታል፡፡ ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  10. ማንኛውም ተጫራች ለኤሌክትሮኒክስ እቃዎች እና ለቶታል እስቴሽን (የቅየሳ መሳሪያዎች) ግዥ በተመለከተ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል የመጫረቻ ሰነዱ በተለያየ ፖስታ በጥንቃቄ በማሸግ ቀበሌ 08 ጋምቢ ጠቅላላ ሆስፒታል ጎን ቢሮ ቁጥር 18 ከተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት አለባቸው፡፡
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በአብክመ መሬት ቢሮ ቢሮ ቁጥር 0-18 በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 220 71 31 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የአብክመ  መሬት ቢሮ

ባህርዳር

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here