በሰሜን ወሎ ዞን የዳዉንት ወረዳ ፍ/ቤት ለአገልግሎት የሚውሉ ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያዎች፣ ሎት 2 የጽዳት እቃዎች፣ ሎት 3 ቋሚ የቢሮ እቃዎች (ኤሌክትሮኒክ) ፣ ሎት 4 ተገጣጣሚ ቋሚ የቢሮ እቃ፣ ሎት 5 የህትመት ዉጤቶች ግዥ መፈጸም ፣ ሎት 6 የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ጥገና እንዲሁም ሎት 7 የተገጣጣሚ የቢሮ እቃዎች ጥገና ለማስጠገን ስለተፈለገ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛትና ማስጠገን ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው፡፡
- የግዥው መጠን ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ መሆን አለባቸዉ፡፡
- ከ1-2 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ሌሎች ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒውን ከኦርጅናል ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- በጨረታ ሰነዱ ላይ ሥርዝ ድልዝ መኖር የለበትም፡፡ ሥርዝ ድልዝ ካለው መስተካከሉ ፓራፍ ይደረግ፡፡
- የሚቀርቡትን እቃዎች ዓይነት ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማሰከበሪያ ዋስትና የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በሲፒኦ ወይም በሞዴል 85 ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በነጻ ከፍ/ቤቱ የዳኝነት ገንዘብ ተቀባይ ባለሙያ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚውልበት 15 ተከታታይ ቀናት ውሰጥ ባሉት ዘወትር የመንግሰት የሥራ ቀናት መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ጨረታዉ የሚዉለዉ ከመጋቢት 02/2018 ዓ/ም ጀምሮ ተከታታይ ለ15 ቀናት ሆኖ እስከ 16ኛው ቀን 8፡00 ድረስ የመጫረቻ ሰነዳቸውን ከተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው በ16ኛው ቀን 8፡00 ታሽጎ 8፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ባይገኙም ጨረታዉ በሰዓቱ ይከፈታል፡፡
- አሸናፊው ተጫራች አሸናፊነቱ እንደተገለፀለት ከ5 ተከታታይ ቀናት በኋላ ባሉት በ5 የሥራ ቀናት ውስጥ ከውል ሰጭ መ/ቤቱ ቀርቦ ባሸነፈበት ገንዘብ መጠን የውል ማስከበሪያ 10 በመቶ በማስያዝ ውል መውሰድ አለበት፡፡
- የጨረታ መዝግያ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጫርተው እራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
- አሸናፊው የሚለየው በጠቅላላ ድምር ውጤት (በሎት) ነዉ፡፡ ተጫራቹ አሽናፊነቱ ተገጾለት ዉል ከፈጸመ በኋላ በውለታው መሰረት እቃውን ሙሉ በሙሉ አጠናቆ በራሱ ወጭ ከመ/ቤቱ ድረስ በማጓጓዝ ማስረከብ ይጠበቅበታል፡፡ አሸናፊው ተጫራች ናሙና ማቅረብ አለበት፡፡
- መ/ቤቱ በግዥ ሂደቱ ላይ 20 በመቶ ከፍና ዝቅ ብሎ የመግዛት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- በዚህ ጨረታ ያልተገለጸ ጉዳዮች አግባብነት ባለው ግዥ ህግ መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 033 241 90 07፣ 033 241 91 13፣ 09 21 27 61 86 በመደወል ተጨማሪ ማብራሪያ ማግኘት ይችላሉ፡፡
የዳዉንት ወረዳ ፍርድ ቤት

