የጨረታ መለያ ቁጥር 873/2018
የአገው ግምጃ ቤት ከተማ አስተዳዳር ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ለቢሮው አገልግሎት የሚውሉ ጠረጴዛ እና ወንበር ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ካላቸው ተጫራቾች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው እንድትሳተፉ ይጋብዛል፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- የግዥው መጠን ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ወይም ቫት ተመዝጋቢነት የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የታደሰ የንግድ ፈቃድ ማረጋገጫ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ ፡፡
- አሸናፊው ድርጅት ቅድመ ግብር ተቀናሽ ሶስት በመቶ ከአሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ ላይ የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ዋና እና ቅጅ በማድረግ ከመጫረቻ ሠነዱ ጋር አያይዘው በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ማቅረብ አለባቸው፡፡ ሲሞላ ያለምንም ስርዝ ድልዝ መሞላት አለበት፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ከታተመበት ቀን ጀምሮ ለ21 ቀናት ይቆያል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ከየካቲት 30/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ21 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ግዥ ፋይ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 02 የጨረታ ሰነዱን ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300 በመግዛት የጨረታ ሰነዱን ግዥ ፋይ/ን/አስ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 02 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና እና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ግዥፋይ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 02 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ስዓት እስከ መጋቢት 21 /2018 ዓ.ም 3፡00 ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግዥ ፋይ/ን/አስ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 02 መጋቢት 21/2018 ዓ.ም 3፡00 ታሽጎ 4፡00 ይከፈታል፡፡ የጨረታ መክፈቻ ቀኑ የህዝብ በአል ወይም ቅዳሜ እና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ስዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሁለት በመቶ በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመስረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ የሚችሉ እና በጥቃቅን የተደራጁ ከሆነ ጥቃቅን ጽ/ቤት የዋስትና ደብዳቤ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የጨረታው አሸናፊ 10በመቶ የውል ማስከበሪያ ውል በሚይዝበት ወቅት ማስያዝ ወይም በጥቃቅን የተደራጁ ከሆነ ስራና ስልጠና ጽ/ቤት የዋስትና ደብዳቤ ማቅረብ አለበት፡፡
- አሸናፊው ድርጅት የሚሰሯቸውን ጠረጴዛ እና ወንበር ስራዎች ማንኛውንም ማቴሪያሎች ወጭ በራሱ አቅርቦ መስራት የሚችል መሆን አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው ፡፡
- የውድድሩ ሁኔታ በሎት ዋጋ ይሆናል፡፡ በተጨማሪ በአብክመ የግዥ መመሪያ ቁጥር1/2003 መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
- የውል ማስከበሪያው ዋስትና ፀንቶ የሚቆየው ውሉ ከሚጠናቀቅበት የመጨረሻ ቀን በኋላ ቢያንስ ለተጨማሪ 30 ቀናት ፀንቶ መቆየት ይኖርበታል፡፡
- አሸናፊው ቅድመ ክፍያ መውሰድ የሚችለው፤ ለሚወስደው ቅድመ ክፍያ ተመጣጣኝ የሆነ መያዣ ወይም ኮላተራል ማስያዝ የሚችል ሲሆን ነው፡፡
- ለተጨማሪ መረጃ የአገው ግምጃ ቤት ከተማ አስተዳዳር ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ ፋይ/ን/አስ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 02 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 224 0724 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
የአገው ግምጃ /ቤ/ከተ/አስ/ገን/ ጽ/ቤት

