በምሥራቅ ጎጃም አስተዳደር ዞን የጎዛምን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ሎት 1. አንድ ብሎክ የመጀመሪያ ምርመራ ክፍል (OPD) እና ሎት 2. አንድ ብሎክ የአርሶ አደር ማሠልጠኛ ማዕከል /FTC/ የግንባታ ሥራዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ፡-
- ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸውና ኮፒውን ከዋጋ መሙያ ሠነዳቸው ጋር ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸውና ኮፒውን ከዋጋ መሙያ ሠነዳቸው ጋር ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የቫት ተመዝጋቢነት ሠርተፊኬት ያላቸውና ማስረጃውን ኮፒውን ከዋጋ መሙያ ሠነዱ ጋር ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ከስራና ከተማ ልማት መምሪያ ሠርተፊኬት የተሠጣቸውና ኮፒውን ከዋጋ መሙያ ሠነዱ ጋር ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን ይዘት እና የስራ ዲዛይን (Bill Of Quantity) ከተዘጋጀው የመደበኛ የጨረታ ሠነድ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል ሰነዱን ጎዛምን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 5 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ከጠቅላላ ዋጋ አንድ ነጥብ አምስት በመቶ በባንክ በተረጋገጠ (ሲፒኦ) በትንሽ ፖስታ በማሸግ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ሲፒኦ ብሎ ማስገባት ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ላይ በእያንዳንዱ ገጽ ማህተማቸውን እና ፊርማቸውን በማስፈር በታሸገ ፖስታ በማድረግ ሰነዱን ለማስገባት ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ለ15 ቀናት ይቆይና በ16ኛው ቀን 3፡30 ታሽጎ በ4፡00 ይከፈታል፡፡ እለቱ የመንግስት ስራ የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- የጨረታ ዋጋ ፀንቶ መቆያ ጊዜ በተመለከተ ጨረታው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር ለ60 ቀናት ፀንቶ ይቆያል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
- ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 058 178 01 30 /058 771 14 22 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
የጎዛምን ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

