ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
42

በጭልጋ ወረዳ ማረሚያ ቤት አስ/ጽ/ቤት ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ቡድን መሪ በበጀት ዓመቱ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ሎት 1 የእህል አቅርቦት፣ ሎት 2 የወጥ ማጣፈጫ፣ ሎት 3 የማገዶ እንጨት፣ ሎት 4 አትክልት ለ6ወር የሚቆይ ተቋሙ ድረስ ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾችን ጽ/ቤቱ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. የዘመኑን የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) የሚያቀርቡ፡፡
  4. የግዥው መጠን ብር 200,000 ( ሁለት መቶ ሺህ ብር) እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ ስለመሆናቸው የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸወ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ የማይመለስ ብር 50 (ሀምሳ ብር) በመክፈል ለግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ቡድን መሪ ቢሮ ቁጥር 02 ድረስ በመምጣት መግዛት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) የጠቅላላ ዋጋውን ቫትን ጨምሮ የሚሞሉትን አንድ በመቶ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ ደረሰኝ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  8. የጨረታው አሸናፊ ድርጅት የአሸነፈውን ጠቅላላ ዋጋ ቫትን ጨምሮ 10 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ ደረሰኝ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  9. የጨረታው አሸናፊ ድረጅት የአሽነፈውን እቃ ጭልጋ ማረሚያ ቤት መጋዝን ድረስ የሚያቀርብ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
  10. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ቅጅዎች ማለትም ዋናውንና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ የጭልጋ ወረዳ ማረ/ቤት አስ/ጽ/ቤት ግዥ ፋይ/ንብ አስ/ ቡድን መሪ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን በተከታታይ ቀናት ከመጋቢት 07/2018 እስከ መጋቢት መጋቢት 21/2018 ዓ/ም እስከ 11፡30 ማስገባት ይኖርበታል፡፡ የጨረታው ሳጥን መጋቢት 22/2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ላይ ይታሸጋል፡፡
  11. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግዥ ፋይ/ንብ አስ/ቡድን መሪ መጋቢት 22/2018 ከረፋዱ 4፡30 ይከፈታል፡፡
  12. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃና ማብራሪያ ከፈለጉ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 09 18 07 24 47 /09 18 22 82 96 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

ማሳሰቢያ፡- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከጨረታ ሰነዱ ላይ ይገኛል፡፡ በሎት የተዘረዘሩት እቃዎች በጥቅል ዋጋቸው አሽናፊው ይለያል፡፡

የጭልጋ ወረዳ ማረሚያ ቤት አስ/ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here