ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
20

በቋራ ወረዳ ገን/ጽ/ቤት የግ/ን/አስ/ቡድን በወረዳው ለሚገኝ ሴ/መስሪያ ቤቶች በ2018 የበጀት ዓመት  አገልግሎት የሚውሉ  ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ፣ ሎት 2 የወተት ፍየል፣ ሎት 3 የእንቁላል ደሮ እንዲሁም ሎት 4 የውሃ ዕቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ አሸናፊ ለይቶ  መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚመለከታቸው ተጫራቾች  መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ እና በዘርፍ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. ግዥው ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች የሚፈለገውን እቃ አይነት ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊክሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ቋራ/ወ/ገን/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 04 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትእዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ በባንክ ዋስትና በመሂ 1 የተቆረጠ ጥሬ ገንዘብ ደረሰኝ ኮፒ አድርገው በፖስታ አሽገው ማስገባት አለባቸው፡፡
  8. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን ቋራ ወ/ገን/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 04 መጋቢት 14/2018 እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም 12፡00 ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች የመወዳደሪያ ሀሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና እና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቋራ ወ/ገን/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን በቀን መጋቢት 29/2018 ዓ/ም 3፡30 ድረስ ማስገባት ይኖርባችኋል፡፡ በዚሁ ሰዓት ይታሸጋል፡፡
  10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቋራ/ወ/ገን/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 በቀን መጋቢት 29/2018 ዓ/ም 4፡00 ይከፈታል፡፡
  1. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
  2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ላይ ስማቸውንና ፊርማቸው የድርጅቱ ማህተም ማስቀመጥ ይኖርባችኋል፡፡
  3. ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ በቀን መጋቢት 29/2018 ዓ/ም 3፡30 ታሽጎ 4፡00 ይከፈታል፡፡
  4. ሎት 2 የወተት ፍየል በቀን መጋቢት 29/2018 ዓ/ም 9፡30 ታሽጎ 10፡00 ይከፈታል፡፡
  5. ሎት 3 የእንቁላል ደሮ በቀን መጋቢት 30/2018 ዓ/ም 3፡30 ታሽጎ 4፡00 ይከፈታል፡፡
  6. ሎት 4 የውሃ ዕቃ በቀን መጋቢት 30/2018 ዓ/ም 9፡30 ታሽጎ 10፡00 ይከፈታል፡፡
  7. አሸናፊው ድርጅት እቃዎችን ቋ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ድረስ በማምጣት ማስከረብ አለበት፡፡
  8. እቃውን የምንረከበው በያዝነው የበጀት ልክ ነው፡፡
  9. አሸናፊ የሚለየው በሎት ነው፡፡
  10. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግዥና ንብረት አስ/ቡድን ወይም ቋራ ወ/ገን/ጽ/ቤት በስልክ ቁጥር 058 271 02 69 /00 31 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

በቋራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here