ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
33

የጎንደር አይራ ጠቅላላ ሆስፒታል አገልግሎት የሚሰጥ መጸዳጃ ቤት በግልጽ ጨረታ አውዳድሮ ከአሸናፊው ድርጅቱ ውል ይዞ ማስገንባት (ማሰራት) ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም  የዘርፉ ተጫራቾች በጨረታው  መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የስራ ደረጃቸውን የሚገልጽ የምስክር ወረቀት ያላቸው፡፡
  4. የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከጎንደር አይራ ጠቅላላ ሆስፒታል ዋና ገንዘብ ያዥ ቢሮ ቁጥር 25 በመምጣት ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) ብቻ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
  7. የሚወዳደሩ ተጫራቾች የስራ ደረጃቸው ከደረጃ -1 እስከ ደረጃ -7 መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
  8. በስራው ከዚህ በፊት ከሚሞሉበት የስራ አፈጻጸም የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ ቢሆን ይመረጣል፡፡
  9. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት የስራውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ በመሂ-1 በመቁረጥ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  10. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን በ2 ፖስታ በማሸግ ዋናና ቅጅ በማለትና በማሸግ ሙሉ ስም፣ የድርጅቱ ማህተም አድራሻውን ከፖስታው ላይ በመፃፍ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት አለባቸው፡፡
  11. ማንኛውም ተጫራች በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በመ/ቤታችን ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባችዋል፡፡ ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን መጋቢት 14/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 21ኛው ቀን 11፡30 ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡ ጨረታው በ22ኛው ማለትም ሚያዚያ 5/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ታሽጎ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  12. ስራው የሚያስፈልገው ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  13. የጨረታ ሰነዱ ሥርዝ ድልዝ ወይም በፍሉድ የተስተካከለ ከሆነ ሰነዱ ተቀባይነት የለውም ወይም መፈረም አለበት፡፡
  14. አሸናፊው በውሉ መሰረትና በወጣው የመሃንዲስ የስራ ዝርዝር መሰረት ሰርቶ የሚያስረክብ ይሆናል፡፡
  15. ተጫራቾቹ ከዚህ በፊት በአገልግሎት አሰጣጥ ቅሬታ ያልቀረበበት መሆን አለበት፡፡
  16. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታው ይካሄዳል፡፡ ጨረታው ሲከፈት ያልተገኙ ተጫራቾች በዕለቱ ለሚተላለፈው ውሳኔ ተገዥ ይሆናሉ፡፡
  17. ጨረታ የሚከፈትበት ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለው  የስራ ቀን ይሆናል፡፡
  18. መስሪያ ቤቱ አሸናፊው ድርጅት ላይ ከተጠቀሱት የስራ ዝርዝር ላይ 20 በመቶ ጨምሮ ወይም ቀንሶ የማሰራት መብቱ እንደተጠበቀ ነው፡፡
  19. መ/ቤቱ አሽናፊውን የሚለየው በጥቅል ድምር ዋጋ ይሆናል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች ሁሉም በጨረታው የተቀመጡትን የሰራ ዝርዝር ዋጋ ሙሉ ለሙሉ በጥንቃቄ መሙላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
  20. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
  21. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ድረስ በአካል በመገኙት ወይም በስልክ ቁጥር 09 18 21 06 28 /09 18 22 05 04 /09 23 22 10 87 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የጎንደር አይራ ጠቅላላ ሆስፒታል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here