ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
34

የጃዊ  የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የግ/ፋ/ንብ/አስ/ቡድን ሂደት ለሆስፒታሉ አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1. እቴሽነሪ  ሎት 2. የደንብ ልብስ፣ ሎት 3. ፈርኒቸር የአገር ውስጥ፣ ሎት 4 የጽዳት እቃ ሎት 5. ህትመት፣ ሎት 6 እና 7 የመኪና ጎማ እነዚህን በዝርዝሩ የተጠቀሱትን እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም መወዳደር የሚችሉ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታከለ (ቫት) ማሰረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. የጨረታ ሰነዱን ዋናውንና ኮፒውን በፖስታ በማሸግ በሁሉም ሰነዶች ላይ የድርጅቱን ህጋዊ ማህተም ሙሉ አድራሻ፣ ስልክ ቁጥር በማስፈር ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  5. አሸናፊው ድርጅት ማሸነፉ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የውል ማስከበሪያ 10 በመቶ ማሰያዝ የሚችሉ፡፡
  6. በጨረታ ሰነዱ ላይ የተዘረዘሩትን እቃዎች ሙሉ በሙሉ ዋጋቸውን ያልሞላ ተጫራች ከጨረታው ውጭ ይሆናል፡፡
  7. የጨረታው አሸናፊ ድርጅት የሚለየው በጠቅላላ ድምር ውጤት ነው፡፡
  8. የጨረታ ማስከበሪያ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ በተመሰከረለት ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ዋጋውን 2 በመቶ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከመጋቢት 14/2018 እስከ መጋቢት 28/2018 ዓ.ም ድረስ ባሉት ተከታታይ ቀናት የጨረታ ሰነዱን ጃዊ/የመ/ደ/ሆ/ግ/ፋ/ንብ/አስ/ደ/የስራ ሂደት መግዛት ይችላሉ፡፡
  10. የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) ብቻ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
  11. የጨረታ ሳጥኑ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት መጋቢት 29/2018 በ8፡00 ታሽጎ መጋቢት 29/2018 በ8፡30 ይከፈታል፡፡
  12. ተቋሙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. ተጫራቾች የጨረታ ዝርዝሩን (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኙት ይችላሉ፡፡
  14. እቃውን ጃ/መ/ደ/ሆስፒታል መካዝን ድረስ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  15. ተቋሙ ጨረታውን ከጠቅላላ ድምር 20 በመቶ የመቀነሰና የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 278 03 05 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የጃዊ  የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here