ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
87

የምሥራቅ ጐጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ ግዥ/ፋ/ንብ/አስ/ደ/የስራ ሂደት አገልግሎት ለሚሰጣቸው ለዞን ፖሊሲ መምሪያ እና ደብረ ማርቆስ አድማ መከላከል ፖሊስ ጽ/ቤት አገልግሎት ለሚሰጡ እቃዎችን ሎት 1. የተሸከርካሪ መለዋወጫ እቃዎች፣ ሎት 2. የተሸከርካሪ የወንበር ልብስ እና ሎት 3 ጀኔሪተር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይገልፃል፡፡

  1. በዘርፉና በዘመኑ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም የግብር መክፈያ መለያቁጥር /ቲን/ ያላቸው፡፡
  2. የግዥው መጠን ብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ወይም በባንክ የተረጋገጠ ሌተር ኦፍ ክሪዲት ወይም በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ለመ/ቤ /ገንዘብ ያዥ በመሂ1 ገቢ ማድረግ አለባቸዉ በእያንዳንዱ ሎት የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ ያላነሰ ከሁለት በመቶ ያልበለጠ ማስያዝ አለባቸዉ፡፡
  4. ተጫራቾች የሞሉትን የጨረታ ሠነድ በጥንቃቄ በማሸግ የግዥ ፈፃሚ መ/ቤቱን የተጫራቹን ስምና አድራሻ በመፃፍ በማህተምና ፊርማ አስደግፎ ለግዥ ፈፃሚ መ/ቤቱ ሠነዱን መመለስ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራቾች የእቃዉን አይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  5. ተወዳዳሪዎች የጨረታ ሠነዱን ግዥ/ፋ/ንብ/አስ/ደ/የስራ ሂደት ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 50 (ሃምሳ ብር) ብቻ በመክፈል ሠነዱን ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ጨረታው የሚከፈተው ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን 4፡00 ተዘግቶ 4፡30 መገኘት በፈለጉ ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ/ በተገኙበት በግልጽ ይከፈታል፡፡ ባይገኙም ጨረታውን ለመክፈት አያስተጓጉልም፡፡
  7. አሸናፊው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ከ5 ተከታታይ የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ 10 በመቶ የውል ማስከበሪያ በማስያዝ ውል ይዞ ያሸነፈበትን /አገልግሎት/ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ 1ኛ ደረጃ የሆነውን በተቀመጠው ስፔስፊኬሽን መሰረት መስጠት አለበት፡፡ ከስፔስፊኬሽኑ ውጭ የሚሰጥ አገልግሎት የማንቀበል መሆኑ ታውቆ ለሚደርስበት ኪሣራ መ/ቤቱ ተጠያቂ አይሆንም፡፡ ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የበዓል ቀን ወይም ዝግ ከሆነ ስዓቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በሚቀጥለው ቀን ይከፈታል፡፡
  8. ዉድድሩ የሚካሄደዉ ሎት (ጥቅል) ዋጋ ሲሆን ሁሉንም አገልግሎትና ሽያጭ ዋጋ መሙላት አለበት፡፡
  9. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 13 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 771 21 46 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

የምሥራቅ ጐጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here