ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
93

በምሥራቅ ጎጃም ዞን ገን/ኢ/ል/ት/መምሪያ የደ/ጥ/ግ/ወረዳ ገን/ኢ/ል/ጽ/ቤት በደባይ ጥላት ግን ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት የቁይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተቋርጦ የቆየውን G+2 ባለ 15 ክፍል የመማሪያ ህንፃ ግንባታ በአልማ በጀት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች

  1. ከላይ በተጠቀሱት የሥራ ዘርፍ የንግድ ሥራ ፈቃድ ፣የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ሰርተፊኬት ፣የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ሰርተፊኬት እና የሙያ ብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማስረጃዎችን ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  2. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻው ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  3. የሚገነባውን ግንባታ የያዘ ዝርዝር መግለጫ ወይም ስፔስፊኬሽን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21ኛው ቀን 11፡30 ድረስ መውሰድ ይኖርባቸውል፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን እስከ 22ተኛው ቀን 3፡30 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከደባይ ጥላት ግን ወረዳ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 3 ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ከዋና ገንዘብ ያዥ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፡፡
  7. ለግንባታው የሚያስፈልገው የሙያ ብቃት ደረጃ 5Bc-Gc እና ከዚያ በላይ መሆን አለባቸው፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦርድ) በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም ብር 500,000 (አምስት መቶ ሽህ ብር) በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  9. አሸናፊ ተጫራች ያሸነፈው ዋጋ የውል ማስከበሪያ 10 በመቶ በጥሬ ገንዘብ ወይም /በሲፒኦ/ ማያያዝ ይጠበቅበታል፡፡ ነገር ግን የሞላው ዋጋ ከመሀንዲስ ግምቱ 25 በመቶ ዝቅ ብሎ ለሞላ ተጫራች ሊያያዝ የሚችለው የውል ማስከበሪያ 25 በመቶ ማያያዝ ይጠበቅበታል፡፡
  10. የጨረታ አሸናፊ መሆን የሚቻለው በጥቅል ዝቅተኛ ዋጋ የሰጠ መሆኑ ታውቆ ለሁሉም አይተሞች በዋጋ መሞላት ይኖርበታል፡፡
  11. ተጫራቾች የጨረታ ሀሳቡን በጥንቃቄ በስም በታሸገ ፖስታ በደ/ጥ/ግ/ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ግዥ ቡድን ክፍል ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ዘወተር በሥራ ስዓት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 22 ተኛው ቀን 3፡30 ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡
  12. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በደ/ጥ/ግ/ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት በ22 ተኛው ቀን 3፡30 ላይ ታሽጎ 4፡00 ጀምሮ የሚከፈት ይሆናል፡፡
  13. የጨረታ መዝጊያና መክፈቻ ላይ በበዓል ቀን ከሆነ ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ስዓት ይሆናል፡፡
  14. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  15. ተጫራቾች የሚሞሉት ሰነድ ላይ ሥርዝ ድልዝ ካለው ጨረታው ውድቅ ይደረጋል፡፡
  16. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 03 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 257 02 57 /01 43 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

የደባይ ጥላት ግን ወረዳ ገን/ኢ/ል/ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here