ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
84

በምዕራብ ጎጃም ዞን በደጋ ዳሞት ወረዳ የፈረስ ቤት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2017 በጀት አመት ለተለያዩ አገልግሎት የሚውሉ  እቃዎችን መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚህም መሰረት ማለትም ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያዎች ፣ሎት2 ወረቀትና የወረቀት ውጤቶችን እና ሎት 3 የህንጻ መሳሪያ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ከአሸናፊው ድርጅት መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በጨረታው ለመወዳደር የምትፈልጉ፡-

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው፡፡
  3. የሚያቀርቡት እቃ ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. የሚገዙት እቃዎች ዓይነት እና ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ / ለሚወዳደሩበት የእቃው ጠቅላላ ዋጋ 2 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ወይም ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም ጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ለእቃዎቹ ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በፖስታ በጥንቃቄ በማሸግ በፈረስ ቤት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በግዥ/ፋ/ንብ/አስ/ቡድን/ ቢሮ ቁጥር 6 በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በሥራ ቀናት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  7. ጨረታው በ16ኛው ቀን 3፡00 ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በፈረስ ቤት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በግዥ/ፋ/ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 6 በ16ኛው ቀን በ3፡30 ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም የመክፈቻ ጊዜው አይራዘምም፡፡
  8. አሸናፊው ድርጅት የአሸነፈውን እቃ ከተቋሙ ንብረት ክፍል ማድረስ የሚችል መሆን አለበት፡፡
  9. ከጨረታ ሰነዱ ላይ ሥርዝ ድልዝ መሆን የለበትም፡፡
  10. ጨረታው የሚዘጋበትና የሚከፈትበት ቀን የህዝብ በዓል ከሆነ በቀጣይ የሥራ ቀን ይከፈታል፡፡
  11. ውድድሩ የሚካሄደው በሎት /ጥቅል ዋጋ ነው፡፡
  12. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በእያንዳንዳቸው የማይመለስ ብር 50 /ሀምሳ ብር / ብቻ በመክፈል ቢሮ ቁጥር 7 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  13. በማስታወቂያ ያልተገለጸ ካለ በግዥ መመሪያ መሰረት ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
  14. ከሎት ውስጥ አንዱን እቃ ካልሞሉ ከውድድሩ ውጭ ይሆናሉ፡፡
  15. ተጫራቾቹ በሰነዱ ላይ የድርጅቱን ስም ፣ማህተም ፣ፊርማ እና አድራሻ አሟልተው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  16. የጨረታው አሸናፊ ውሉን ከወሰደበት ቀን ጀምሮ እቃዎችን በ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
  17. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
  18. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ በፈረስ ቤት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግዥ/ፋ/ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 6 በአካል በመቅረብ ወይም በ09 12 79 78 12 /09 20 77 22 08 /09 10 67 87 33 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

የፈረስ ቤት ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here