በደቡብ ጎንደር አስተዳደር ዞን የነፋስ መውጫ ከተማ አስ/ከተማና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ የሚደነግገው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀፅ 8/1 መሰረት በ2017 በጀት አመት ለ3ኛ ዙር ጨረታ ለመኖሪያ ብዛት 20 ፣ለድርጅት 5 እና በማኒፋክቸሪግ ብዛት 3 አጠቃላይ 28 ቦታዎችን በጨረታ ለተጠቃሚዎች ማስተሳሰፍ ይፈለጋል፡፡ በመሆኑም፡-
- መጫረት የሚፈልጉ ማንኛውም ሰው ወይም ድርጅት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የቦታውን ዝርዝር መረጃ እና የጨረታ ሰነድ የማይመሰስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ቢሮ ቁጥር 3 በመምጣት መግዛት ይቻላል፡፡
- የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ ቀኑ 11፡30 ብቻ ለዚህ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ በቢሮ ቁጥር 3 ማስገዛት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው የሚዘጋው በ10 ኛው ቀን በ11፡00 ይሆናል፡፡
- ጨረታ የሚከፈተው ከተዘጋበት ቀን ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን በ3፡00 ሁሉም ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ካልሆነም ተወካዮችም ሆነ ግለሰቦቹ ባይገኙም ጨረታው የሚከፈት ሲሆን ጨረታው የሚከፈትበት ቦታ በተመለከተ በነ/መ/ቀበሌ 03 ኢ/ል/ከ/አገ/ጽ/ቤት ይሆናል፡፡
- ይህ ማስታወቂያ ተግባራዊ የሚሆነው ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀን ይሆናል፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር ሁኔታ በጽ/ቤቱ የማስታወቂያ ሰሌዳ ወይም በስልክ ቁጥር 058 445 01 92 ወይም 058 445 13 60 ደውለው ማግኘት ይቻላል፡፡
- ሌሌች ተጨማሪ ዝርዝር ሃሳቦችን /ህጎችን/ ከሚሸጠው ሰነድ ማገኘት ይችላሉ፡፡
- መ/ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የነፋስ መውጫ ከተማ አስ/ከተማና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት