የግዥ መለያ ቁጥር ግ/ጨ/04/2017
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሲቪል ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ኮሚሽን/ፑል/፣ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ጨምሮ ለ2ቱም መ/ቤቶች ለ2018 በጀት አመት አመታዊ የቢሮ ህንፃ እና ምድረ ግቢ የጽዳት አገልግሎት እና የተሽከርካሪ መለዋወጫ አቅርቦት ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ሀ/ የጽዳት አገልግሎት በጨረታዉ የሚሳተፉ በአነስተኛና ጥቃቅን ኢተርፕራይዝ ተደራጅተዉ ከትምህርትና ስልጠና ተቋም ማስረጋጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡ ለ/ የተሽከርካሪ መለዋወጫ አቅርበት የሚሣተፋ የባሕር ዳር ከተማ ላይ መደብር ወይም ወኪል መኖሩን ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ ሆነው የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- የግዥው መጠን ብር 200,000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገዙ ዕቃዎችና የአገልግሎት ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የተሽከርካሪ መለዋወጫ የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ከግዥና ፋይ/ንብ/አስተ/ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 007 ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ16 ተከታታይ ቀናት ማግኘት ወይም መግዛት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የጥቃቀን የድጋፍ ደብዳቤ በማምጣት ከግዥና ፋይ/ንብ/አስተ/ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 007 ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ16 ተከታታይ ቀናት ማግኘት ወይም መግዛት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ከአነስተኛና ጥቃቅን ኢተርፕራይዝ የዋስትና ደብዳቤ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በማድረግ በአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ከግዥና ፋይ/ንብ/አስተ/ዳይሬክቶሬት በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ጨረታው ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት በ16ኛው ቀን አስከ 8፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 007 በ16 ተኛው ቀን 8፡00 ተዘግቶ በ 8፡30 ይከፈታል፡፡ ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በ8፡00 ተዘግቶ በ8፡30 ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 007 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 220 96 44 /058 220 96 46 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
- አዲስ ከተቋቋሙት ኢንተርፕራይዞች ዉጭ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
የአብክመ ሲቪል ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ኮሚሽን/ፑል/
ባህርዳር