ሳምኬት ኮንስትራክሽን በሰሜን ሸዋ ዞን በቃብትያ ቡልጋ ከተማ አስተዳደር ቱለፋ ቀበሌ ልዩ ቦታው ኢግዱ ለገዱባ ተብሎ በሚጠራው ቦታ የጥቁር ድንጋይ ማዕድን ማምረት ሥራ ፈቃድ እንዲሰጣቸው መሥሪያ ቤታችንን ጠይቀዋል፡፡
የጂኦግራፊክ ኮኦርዲኔቶችም፡-
Adindan UTM Zone 37N
Geographic Coordinates of the license area
Block:-1
Corner | Easting | Northing |
1 | 526514.5071 | 1023772.4165 |
2 | 526839.7511 | 1023776.7613 |
3 | 526588.0275 | 1024045.9800 |
4 | 526381.0888 | 1023917.5604 |
በሰሜን | በደቡብ | በምዕራብ | በምሥራቅ |
ምሌት ትሬዲንግና ኤግዱ ለገዲባ የጥቁር ድንጋይ ማምረቻ | እነ አለማየሁ | ትክክል ይመር አበጋዝ የጥቁር ድንጋይ ማዕድን ማምረት | እነ ሸዋቀና እና ሸዋንግዛው |
ስለዚህ የተጠየቀውን ፈቃድ ከመስጠታችን በፊት በተጠቀሰው አካባቢ በተለይም ከዚህ በላይ በተመለከቱት የጂኦግራፊክ ኮኦርዲኔቶች በሚከለል ቦታ ላይ ይገባኛል የሚል ካለ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሰባት /07/ ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን በጽሑፍ ለመሥሪያ ቤታችን እንዲያቀርብ እናሳስባለን፡፡ ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058 222 12 37/21 42 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የአብክመ ማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ