ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
59

ለወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ የጽዳት እቃዎች ፣ህትመቶች እና የጽህፈት መሳሪያዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት እና ማሳተም ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በጨረታ ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተወዳዳሪዎች በሙሉ

  1. ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያላቸው እና የዘመኑን ግብር የከፈላችሁ፡፡
  2. ንግድ ፈቃዱና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎች ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መታሸግ አለበት፡፡ ተጫራቾች የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ብር ከ200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፡፡
  3. የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናል ፖስታ በማሸግ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  4. ከጨረታ ሰነዱና ከታሸገ ፖስታ ላይ የድርጅት ማህተም ተነባቢ በሆነ መልኩ መቀመጥ ይኖርበታል፡፡
  5. ተጫራቾች ያሸነፉበት የስራ (የእቃ) ዋጋ ድምር 10,000 /አስር ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ 2 በመቶ ተቀንሶ ለመንግስት ገቢ ይሆናል፡፡ መ/ቤቱ ቫት በመመሪያው መሰረት ይሰበስባል
  6. ተጫራቾች የሞሉትን የዋጋ 1 በመቶ በጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ/ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወይም ከተፈቀደላቸው ባንከ በተመሰከረለት /ሲፒኦ/ በማሲያዝ ከፖስታው ውስጥ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  7. የጨረታ ሰነዱን በወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግዥ ኦፊሰር ቢሮ 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይቻላል፡፡
  8. ጨረታውን ማሸነፋቸው ከተነገራቸው በኋላ ማሻሻያ ማድረግ እና ከጨረታ እራሣቸውን ማግለል አይቻልም፡፡
  9. የጨረታ ሰነድን ዝርዝር ማብራሪያ ከጨረታ ሰነድ ማግኘት ይቻላል፡፡
  10. ተጫራቾች የአማራ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ያወጣውን ግዥ አፈጻጸም መመሪያ አዋጅ ቁጥር 1/2003 እና ተሻሽለው ለወጡ መመሪያዎችና አዋጆች ተገዥ መሆን ይገባቸዋል፡፡
  11. የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ከ30/10/2017 ዓ.ም እስከ 20/11/2017 ዓ.ም ድረስ ባሉት ተከታታይ ለ21 ቀናት በወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግዥ ኦፊሰር ቢሮ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን እስከ 3፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባችኋል፡፡ የጨረታ ሳጥኑ በ 20/11/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ታሽጎ የጨረታ ሳጥኑ በዚህ ዕለት ከጠዋቱ 3፡30  ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመመሪያው መሰረት የሚከፈት ይሆናል፡፡
  12. ተጫራቾች ጨረታ በሚከፈትበት ወቅት ባይገኙም በመመሪያው መሰረት ይከፈታል፡፡
  13. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  14. ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በሥራ ሂደቱ ስልክ 033 331 01 72 እና 033 331 02 52 ደወሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
  15. የጨረታ መክፍቻ ቀን በዓል ከሆነ ወደ ሚቀጥለው የሥራ ቀን ይተላለፋል፡፡
  16. አሸናፊው ማሸነፉ ተነግሮት ውል ከወሰደ በኋላ ሆስፒታሉ በሚያዘው መሰረት ገዝቶ ማቅረብ አለበት፡፡
  17. አሸናፊው ድርጅት ውለታ ከወስደበት ቀን ጀምሮ እስከ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ሲታዘዝ ማቅረብ አለበት፡፡
  18. የተጠቀስውን ግብዓት በጨረታ አሽናፊው ወጭውን ችሎ የሚቀርብ ይሆናል፡፡
  19. ወድድሩ በሎት ድምር ነው፡፡

የወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here