ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
44

በባሕር ዳር ከተማ የፋሲሎ ክፍለ ከተማ የውሃ ቱቦ ፣የውሃ ሆዝ እና በመስመር ጤፍ መዝሪያ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ የተሻለ ዋጋ ላቀረቡ ተወዳዳሪዎች መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  1. ተጫራቾች የሚገዙትን እቃ በአካል ፋሲሎ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በመምጣት ማየት ትችላላችሁ፡፡
  2. የጨረታ ሰነዱን ቢሮ ቁጥር 9 በብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመግዛት መውሰድ ይችላሉ፡፡
  3. አሸናፊው የሚለየው በጠ.ድምር /በሎት/ ዋጋ ይሆናል፡፡
  4. የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ብር /ዕቃ/ ጠቅላላ ዋጋ ብር 10,000 / አስር ሽህ ብር/ ብቻ በባንክ የተረጋገጠ ክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በመ/ቤቱ መ/ሂ1 በማስያዝ የከፈሉበትን ደረሰኝ ኮፒ በማድረግ ከመወዳደሪያ ሰነዱ ጋር መቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ጨረታው ከተለየ በኃላ አሸናፊው ድርጅት ካሸነፈው ጠቅላላ ዋጋ 25 በመቶ የውል ማስከበሪያ ማስያዝ አለበት፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሀሳባቸዉን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ፋሲሎ ክፍለ ግ/ፋ/ን/አስ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 9 ጨረታዉ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ሰነድ ማስገባት ይችላሉ፡፡
  7. ጨረታው በ16ተኛው ቀን 4፡30 ታሽጎ በ5፡00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  8. ስለጨረታው አከፋፈት ቅሬታ ያለው ተጫራች ካለ ጨረታው ከተከፈተ ቀን ጀምሮ ባለው 5 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ማቅረብ ይቻላል፡፡
  9. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 9 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 222 15 66 በመደወል መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡
  10. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  11. ተጫራቾች ተወዳድረው ካሸነፉ በኋላ እራሳቸውን ከጨረታው ማግለል አይችሉም፡፡

የፋሲሎ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here