ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
35

ጎንደር አይራ ጠቅላላ ሆስፒታል ለሰራተኞች ሰርቪስ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ የመኪና ኪራይ ለመከራየት በግልጽ ጨረታ አውዳድሮ ከአሸናፊው ድርጅቱ ውል ይዞ በየወሩ እየከፈለ ከመስከረም ወር ጀምሮ ለ10 /አስር ወራት/ ተከራይቶ አገልግሎት ማሰጠት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ የመኪና አከራይ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡

  1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የባለቤትነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት /ሊቭሪ/ ያላቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትን የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ በመሂ-1 በመቁረጥ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን በ2 ፖስታ በማሸግ ዋናና ቅጅ በማለት ሙሉ ስም፣የድርጅቱ ማህተም፣አድራሻውን ከፖስታው ላይ በመፃፍ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት አለባቸው፡፡
  7. ማንኛውም ተጫራች በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በመ/ቤታችን ግ/ፋ/ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል ፤ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ከነሐሴ 5/2017 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን 11፡30 ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡ ጨረታው በ16ኛው ቀን ማለትም ነሐሴ 20/2017 ዓ.ም 4፡00  ታሽጎ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
  8. የምንከራየውን ተሸከርካሪ አይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  9. የጨረታ ሰነዱ ሥርዝ ድልዝ ወይም በፍሉድ የተስተካከለ ከሆነ ሰነዱ ተቀባይነት የለውም ወይም መፈረም አለበት፡፡
  10. አሸናፊው ከጨረታ ሰነዱ ከተጠቀሰው የሥራ ስዓት ውጭ የግል ስራቸውን የማከናወን መብት አላቸው፡፡
  11. የውል ጊዜው ሲያበቃ በአከራይና ተከራይ የጋራ መግባባት አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ለተጨማሪ ጊዜ የሚራዘም ይሆናል፡፡
  12. ለተሸካርካሪው የሚያስፈልጉ የነዳጅ፣የዘይትና ቅባት፣የጎማ፣የሹፌር፣ የጥገናና ሌሎች ወጭ በአከራይ የሚሸፈን ይሆናል፡፡
  13. ተጫራቾች ከዚህ በፊት በአገልግሎት አሰጣጥ ቅሬታ ያልቀረበባቸው መሆን አለበት፡፡
  14. ተሸከርካሪው ወደ ሥራ ሲገባ ደህንነቱ በባለሙያ ተፈትሾ ሥራ የሚጀምር ይሆናል፡፡
  15. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታው ይካሄዳል ፤ጨረታው ሲከፈት ያልተገኙ ተጫራቾች በዕለቱ ለሚተላለፈው ውሳኔ ተገዥ ይሆናሉ፡፡
  16. የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመ/ቤታችን ዋና ገ/ያዥ ማካኝነት በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
  17. ክፍያ በሚፈጸምበት ወቅት በስማቸው (በድርጅቱ) የተሰራ ህጋዊ ደረሰኝ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  18. ከአማካይ የገቢያ ጥናት ዋጋ በላይ የሞላ ተጫራቾች ከጨረታ ውጭ ይሆናሉ፡፡
  19. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ብሄራዊ በዓል ከሆነ ለሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል፡፡
  20. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
  21. ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 09 22 23 10 87 /09 18 22 05 04/ 09 18 21 06 28 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የጎንደር አይራ ጠቅላላ ሆስፒታል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here