ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
46

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ገንዘብ መምሪያ የምሥራቅ በለሣ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በመደበኛው በጀት በምሥራቅ በለሣ ወረዳ ሥር ላሉ መኪና ላላቸዉ ሴ/መ/ቤቶች አገልግሎት የሚዉል አመታዊ የመኪና እቃዎችን (መለዋወጫ) እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም የሚቆይ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ዉል በመስጠት ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡ ሰለሆነም መወዳደር ለምትፈልጉ ድርጅቶች በሙሉ የጨረታ ሰነዱን በምሥራቅ በለሣ ወረዳ ግዥና ንብ/አስ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 16 በመቅረብ የማይመለስ ብር 400 (አራት መቶ ብር) ብቻ በመግዛት መወዳደር የምትችሉ ሲሆን የጨረታው መሥፈርትም፡-

  1. በዘርፉ የታድሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና የግብር ከፋይ የምዝገባ ሰርትፊኬት (ቲን) ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  2. የተጨማሪ ሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ እና ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) እና ከዚያ በላይ የሆኑ፡፡
  3. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን 0.5 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ (ሲፒኦ) በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታው የሚገቡትን ውለታ በአግባቡ የሚፈጽሙ መሆን አለባቸው፡፡
  5. ማንኛውም ተጫራች ሌላ ተጫራች በሰጠው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ማቅረብ አይችልም፡፡
  6. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዶችን በታሸገ ኢቨሎፕ ጨረታዉ በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታ ቀናት ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይችላሉ፡፡
  7. ጨረታው ለ15 ቀን በጋዜጣ ወቶ ከቆየ በኋላ በ16ኛዉ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ተዘግቶ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በይፋ ይክፈታል፤ እንዲሁም ተጫራቾችና ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታው የሚከፈት ይሆናል፡፡
  8. የታዘዘው የመኪና እቃ በበጀት እጥረት ምክንያት አንሶ ሳይገዛ ቢቀር ጽ/ቤቱ የማይገደድ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
  9. መ/ቤቱ ጨረታውን የተሻለ አማራጭ ካገኘ ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  10. ጨረታዉ በሚከፈትበት ቀን በዓል (ካላንደር) ከሆነ በሚቀጥለዉ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  11. የቅሬታ ቀን ጨረታዉ ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የሥራ ቀናት ማቅረብ ይችላሉ፡፡
  12. የጨረታው አሸናፊ የሚለየው  በሞሉት ጥቅል ድምር ዝቅተኛ ዋጋ  የሞላውን ድርጅት ነው፡፡
  13. ተጨማሪ መረጃ መጠየቅ ከፈለጉ ምሥራቅ በለሣ ወረዳ ግዥና ንብ/አስ/ ቡድን ቢሮ ቁጥር 16 በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 058 339 00 04 /01 16 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
  14. የጨረታ ሰነዱ ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ25 ተከታታይ ቀናት ዋጋው ፀንቶ የሚቆይ ይሆናል፡፡
  15. ጨረታው ከተዘጋ በኋላ የሚቀርብ ማንኛውም የመጫረቻ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
  16. ድርጅቱ ጨረታዉ ሲከፈት ከፖስታዉ ላይ ማህተሙን፣ ሥም እና ፊርማዉን ማስቀመጥ አለበት፡፡
  17. የሚገዙት (የሚቀርበዉ የመኪና መለዋወጫዎች) አሸናፊዉ ድርጅት እስከ ጎንደር ከተማ ጋራጅ ድረስ በራሱ ወጭ ማቅረብ የሚችል፡፡
  18. የሚቀርቡት እቃዎች በስፔስፊኬሽኑ መሰረት ኦርጅናል መሆን አለባቸዉ፡፡
  19. አሸናፊዉ ድርጅት ያሸነፋቸዉን እቃዎች ጽ/ቤታችን በሚፈልግበት ጊዜና ቦታ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወዲያዉኑ ማቅረብ የሚችሉ፡፡

የምሥራቅ በለሣ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here