የመጀመሪያዉ ጋዜጣ በኢትዮጵያ

0
40

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ጋዜጣ “ዓዕምሮ” በ1900 ወይም በ1901 ዓ.ም ነው የተጀመረው:: ጋዜጣው አራት ገፆች ነበሩት:: በሣምንት አንድ ጊዜ ቅዳሜ ነበር ህትመቱ:: ጋዜጣው በእጅ ተገልብጦ በ24 ቅጂ ይሰራጭም ነበር- ለቤተመንግሥት ቅርብ ለሆኑ መሣፍንት እና መኳንንቱ::

በጋዜጣው ሽፋን የሚያገኙት ወይም ትኩረት የሚደረግባቸው በቤተመንግሥት ዙሪያ የሚከናወኑ  እና ሀይማኖታዊ ሁነቶች ነበሩ::

በ1905 ዓ.ም  ደግሞ በአዲስ አበባ በተከፈተው ማተሚያ ቤት እየታተመ የጋዜጣው ቅጂ ብዛት ከ200 በላይ ደርሶ ነበር:: በ1906 ህትመቱ እስከ ተቋራጠበት ጊዜ ድረስ::

ኋላም ህትመቱ እንደገና ቀጥሎ ከ1924 እስከ 1935 ዓ.ም ወቅታዊውን የአውሮፓውያን አገራት ግንኙነት እና የኢትዮጵያን አንድነት የሚሰብኩ፣ የንጉሳዊ ቤተሰቦች ጋብቻ እና ልደት ወ.ዘ.ተ ሲስተናገዱበት ቆይተዋል::

ከሐምሌ 1935 ዓ.ም በኋላም ጣሊያን ኢትዮጵያን ለመውረር የነበራትን ምኞት የሚያጋልጡ ጽሁፎች ለንባብ በቅተውበታል- በዓዕምሮ::

ምንጭ ፡- ሊንክዲን ድረ ገጽ፡፡

(ታምራት ሲሳይ)

በኲር የነሐሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ዕትም

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here