ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
17

በምዕራብ ጐንንደር ዞን የዳሞት የገ/ሁሉ/ህ/ስ/ማ/ዩኒዬን ኃ.የት የ2017 ዓ.ም ምርት ዘመን ነጭ በቆሎ ሎት 1 – 5,000 ኩ/ል ሎት 2 – 5,000 ኩ/ል ሎት 3 – 10,000 ኩ/ል በተጨማሪም ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የG+5 ለህንጻ የሚያስፈልጉ እቃዎች ማለትም ሎት 1 ፈርንቸር ከነመገጣጠሙ፣ ሎት 2 የመጋረጃ ቁሳቁስ ከነጁ፣ ሎት 3 የሳውንድ ሲስተም እስከመገጣጠሙ እና ሎት 4 ላይት ቦክስ (ዲጅታል ታፔላ) እስከመገጣጠሙ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት መሸጥ ይፈልጋል፡፡ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች ሁሉ መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘርፍ የታደሰ የንግድ የሥራ ፈቃድ ያላቸዉና እና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
  2. የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፊኬት ያላቸው፡፡
  3. የጨረታው ዋጋ ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ የምስክር ወረቀት ማስያዝ እና የሚሞሉት ዋጋ የቫት ግብይት ከሆነ ከነቫቱ መሆን አለበት፡፡
  4. ከላይ የተዘረዘሩትን የምታሟሉ ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ከዩኒየኑ ዋና መሥሪያ ቤት ቢሮ ቁጥር 1/ሂሳብ ክፍል እስከ መጨረሻው ቀን 8፡00 ድረስ መውሰድ ይችላሉ፡፡
  5. የጨረታ ሰነዱን በኦርጅናል የማወዳደሪያ ዋጋ በመሙላት በድርጅቱ ማህተም በተዘጋጀ ፖስታ በማሸግ በተዘጋጄው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፤ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለበቆሎ በ8ኛው ቀን 8፡00 ተዘግቶ 8፡30 የሚከፈት ይሆናል፡፡ ለG+5 ህንጻ እቃዎች በ11ኛው ቀን 8፡00 ተዘግቶ በዚሁ ቀን በ8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች ባሉበት ይከፈታል፡፡
  6. የንግድ ፈቃዱ ወይም የድርጅቱ ስምና የክብ ማህተሙ ስም ተመሳሳይ መሆን ሲኖርበት እዲሁም የጨረታውን ቅጽ የሚሞላው ሰው ሥም ከላይ ከተጠቀሱት ጋር ተመሳሳይ መሆን አለበት፡፡
  7. ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታው አይስተጓጐልም፡፡
  8. የጨረታ ማስከበሪያ ከጠቅላላ ዋጋ 2 በመቶ (ሲፒኦ) ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡
  9. አሸናፊው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ድምር 10 በመቶ በማስያዝ ውል መያዝ አለበት፤ ይህንን ካላደረገ ግን ለጨረታ ማስከበሪያ የተያዘው ብር ለድርጅቱ ገቢ ይሆናል፡፡
  10. ዩኒዬኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  11. በዚህ ያልተጠቀሱት ሀሳቦች ቢኖሩ በዩኒየኑ ግዥና ሽያጭ መመሪያ መሠረት የሚሰተናገድ ይሆናል፡፡
  12. የማስረከቢያ ቦታ ዳሞት ሁለ/የገ/ህ/ስ/ማ/ዩኒየን ኃየተ ቡሬ 03 ቀበሌ ከሚገኘው ዋና ቢሮ ይሆናል፡፡
  13. ተጫራቾች ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 058 774 06 40 /10 32 በመደወል ወይም በአካል በመገኘት መስተናገድ ይችላሉ፡፡
  14. በቆሎ የማንሻ ቦታ ቡሬ 04 ቀበሌ ሆኖ የ10,000 – 30 ቀን 5000 ኩ/ል በየራሱ 15 ተከታታይ የሥራ ቀናት ይሆናል፡፡

የዳሞት የገ/ሁሉ/ህ/ስ/ማ/ዩኔዬን ኃየት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here