በጭልጋ ወረዳ ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጽ/ቤት ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ቡድን መሪ በበጀት ዓመቱ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን እቃዎች ማለትም ሎት 1 የእህል አቅርቦት፣ ሎት 2 የወጥ ማጣፈጫ፣ ሎት 3 የማገዶ እንጨት፣ ሎት 4 አትክልት፣ ሎት 5 የምግብ ዘይትእና ፊኖ ለ6 ወር ሚቆይ ከተቋሙ ድረስ የሚያቀርብ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- የዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) የሚያቀርቡ፡፡
- የግዥው መጠን ብር 200,000 (ሁለት ሺህ ብር) እና ከዚያ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገቡ ስለመሆናቸው የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ብቻ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸወ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ የማይመለስ ብር 50 (ሃምሣ ብር) በመክፈል ለግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ቡድን መሪ ቢሮ ቁጥር 02 ድረስ በመምጣት መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) የጠቅላላ ዋጋውን ቫትን ጨምሮ የሚሞሉትን አንድ በመቶ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፕኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ ደረሰኝ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የጨረታው አሸናፊ ድርጅት የአሸነፈውን ጠቅላላ ዋጋ (ቫትን) ጨምሮ 10 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፕኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ ደረሰኝ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የጨረታው አሸናፊ ድረጅት የአሸነፈውን እቃ ጭልጋ ማረሚያ ቤት መጋዝን ድረስ የሚያቀርብ፡፡
- ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ቅጅዎች ማለትም ዋናውንና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ የጭልጋ ወረዳ ማረሚያ ቤት አስ/ጽ/ቤት ግዥ/ፋይ/ንብ/አስ/ቡድን መሪ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን በተከታታይ ቀናት ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከነሐሴ 26/2017 እስከ መስከረም 05/2018 ዓ/ም እስከ 11፡30 ማስገባት ይኖርበታል፤ የጨረታው ሳጥን መስከረም 06/2018 ዓ ም ከጠዋቱ 4፡00 ላይ ይታሸጋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ቡድን መሪ መስከረም 06/2018 ከጠዋቱ 4:30 ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃና ማብራሪያ ከፈለጉ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 09 18 07 24 47 /09 38 51 20 12 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
ማሳሰቢያ፡-
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከጨረታ ሰነዱ ላይ ይገኛል፡፡
- በሎት የተዘረዘሩት እቃዎች በጥቅል ዋጋቸው አሸናፊው ይለያል፡፡
የጭልጋ ወረዳ ማረሚያ ቤት አስ/ጽ/ቤት