በወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለ2018 ዓ.ም በጀት አመት በሆስፒታሉ ውስጥ ተመድበው ለሚሰሩ ሰራተኞች እስከ 61 ሠው የሚጭን የህዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ብዛት 2 የሆኑ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል፡፡
- ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን)ያላቸው እና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
- ንግድ ፈቃድና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎች ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ መታሸግ አለበት፤ ተጫራቾች የሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ከብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባችው፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናል በፖስታ በማሸግ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ከጨረታ ሰነዱና ከታሸገው ፖስታ ላይ የድርጅት ማህተም ተነባቢ በሆነ መልኩ መቀመጥ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች የኪራይ ሥራ ዋጋ ድምር 20,000 (ሃያ ሺህ ብር) በላይ ከሆነ 3 በመቶ ተቀንሶ ለመንግስት ገቢ ይሆናል፤ መ/ቤቱ ቫት ይሰበስባል፡፡
- ግዥ ፈፃሚው መ/ቤት በጨረታ ሰነዱ ከተዘረዘሩት ሥራዎች 20 በመቶ የመጨመርና የመቀነስ መብት አለው፡፡
- ተጫራቾች የሞሉትን የሥራ ዋጋ 2 በመቶ በጨረታ ማስክበሪያ (ቢድ ቦንድ) በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወይም ከተፈቀደላቸው ባንክ በተመሰከረለት (ሲፒኦ) በማስያዝ ከፖስታው ውስጥ በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን በወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግዥ ኦፊሰር ቢሮ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- ጨረታውን ማሸነፋቸው ከተነገራችው በኋላ ማሻሻያ ማድረግ እና ከጨረታ ራሣቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ዝርዝር ማብራሪያ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የአማራ ክልል ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ያወጣውን ግዥ አፈጻጸም መመሪያ አዋጅ ቁጥር 1/2003 እና ተሻሽለው ለወጡ መመሪያዎችና አዋጆች ተገዥ መሆን ይገባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነድ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ከነሀሴ 26/2017 ዓ.ም እስከ መስከረም 17/2018 ዓ.ም ድረስ ባሉት ተከታታይ ለ22 ቀናት በወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግዥ ኦፊሰር ቢሮ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን እስከ 3፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሳጥኑ ነሀሴ 17/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ታሽጎ በዚህ ዕለት ከጠዋቱ 3፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመመሪያው መሰረት የሚከፈት ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታ በሚከፈትበት ወቅት ባይገኙም በመመሪያው መሰረት ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በሥራ ሂደቱ ሥልክ ቁጥር 033 331 02 52 ደወሎ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
- የጨረታ መክፍቻ ቀን በዓል ከሆነ ወደ ሚቀጥለው የሥራ ቀን ይተላለፋል፡፡
- ውድድሩ በሎት ድምር ነው፡፡
- የመኪና ሥራ ወጭ ለሹፌር፣ ለነዳጅ በተመለከተ እና ሌሎች የሚያስፈልጉ ወጭዎች አሸናፊው ይሸፍናል፡፡
- አሸናፊው ማሸነፉ ተነግሮት ውል ከወሰደ በኋላ ሆስፒታሉ በሚያዘው ቦታ ደርሶ መልስ ሰርቢስ መስጠት አለበት፡፡
- አሸናፊው ድርጅት ውለታ ከወስደበት ቀን ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ሆ/ሉ ሥራ ብሎ ሲያዘው በታዘዘው ቀን ውስጥ የሰራተኞች ሰርቢስ መስጠት አለበት፡፡
የወልዲያ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል