በደቡብ ጎ/ዞን የእብናት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አገልግሎት የሚውል APTS/AUDITABLE PHARMACUTICAL TRANSACTIONS SERVICE/ የአለሙኒየም ስራ በጋዜጣ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላችሁ፡፡
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ያላቸው፡፡
- ግዡ ከ200,000 / ከሁለት መቶ ሺህ/ ብር እና ከዚያ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
- ከአሁን በፊት APTS/ AUDITABLE PHARMACUTICAL TRANSACTIONS SERVICE/ ስራ መስራቱን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ሙሉ ቁሳቁሶችን ራሳቸው በማቅረብ መስራት የሚችሉ፡፡
- የንግድ ፈቃድ አይነት የአልሙኒየም ስራ ፈቃድ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚችሉ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 500.00 /አምስት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል በእ/የመ/ደ/ሆ/ግ/ፋ/ን/አስ/ደ/የስራ ሂደት ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የሚመለስ የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን 2በመቶ በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተረጋገጠ /ሲፒኦ/ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናል እና ኮፒ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ውስጥ አድርጎ እመደሆ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ሆስፒታሉ የሚያሰራውን ስራ 20በመቶ የመጨመርና የመቀነስ መብት አለው፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ የቀረቡትን የስራ አይነቶች ሙሉ በሙሉ መሙላት አለባቸው አንድም ስራ አለመሙላት ከውድድር ውጭ ያደርጋል፡፡
- የሚሰሩትን የስራ አይነቶች /ስፔስፍኬሽን/ መግለጫ ከጨረታ ሰነድ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሰነዱ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከታተመበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ይቆያል፡፡
- ሆስፒታሉ አሸናፊውን በጥቅል ዝቅተኛ ዋጋ ይመርጣል፡፡
- ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው/ ቢገኙም ባይገኙም በ16ኛው ቀን ይከፈታል፡፡ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የህዝብ በዓላት ከሆነ በቀጣዩ በስራ ቀን ከቀኑ 8፡00 ታሽጎ በ8፡30 ይከፈታል፡፡
- ሆስፒታሉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጫራቾች በመጫረቻ ሰነዱ ላይ ስትሞሉ ስርዝ ድልዝ (በፍሉድ) የጠፋ መኖር የለበትም ፡፡
- አሸናፊው ተጫራች በስሙ የታተመ ህጋዊ ደረሰኝ ያለው መሆን አለበት፤ደረቅ ቸክ ማስያዝ አይቻልም፡፡
- አሸናፊው አሸናፊነቱ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ከ5 የስራ ቀናት በኃላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የውል ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን 10 በመቶ በእብናት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስም በባንክ በተረጋገጠ ወይም በጥሬ ገንዘብ ብቻ በማስያዝ ውል መውሰድ አለባቸው፡፡
- ጨረታው ከተዘጋ በኃላ የሚቀርብ የመጫረቻ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
- በተለያዩ ምክንያቶች የጨረታ ሰነዱ ችግር ቢኖርበት ማሰታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 (አስር)ተከታታይ ቀናት ውስጥ ማስተካከያ የሚደረግበት ይሆናል፡፡
- በዚህ ሰነድ ያልተገለፀ ሀሳብ ቢኖር በግዥ መመሪያው መሰረት ተግባራዊ ይሆናል፡፡
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ፡፡በስልክ ቁጥር 0584400913 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የእብናት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል