በአፈ/ከሳሽ ቸኮል ጥናው እና በአፈ/ተከሳሽ አስማረ ገረም መካከል ስላለው የአፈጻጸም ክስ ክርክር ጉዳይ የአፈ/ተከሳሽ ንብረት የሆነው በቲሊሊ ከተማ 02 ቀበሌ የሚገኝ አዋሣኙም በምሥራቅ አስማረ ገረም፣ በምዕራብ መንገድ፣ በሰሜን ንጉሴ ወርቅነህ እንዲሁም በደቡብ የልቤ ዘለቀ የሆነ ስፋቱ 250 ካ/ሜ ቤትና ቦታ በመነሻ ዋጋ ብር 1,325,620.75 /አንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሃያ አምስት ሺህ ስድስት መቶ ሃያ ብር ከሰባ አምስት ሳንቲም/ በማድረግ ከጥቅምት 10/2018 ዓ/ም አስከ ህዳር 10/2018 ዓ/ም ድረስ በጋዜጣ ወጥቶ ቆይቶ ህዳር 11/2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 2፡30 – 6፡30 በጨረታ ስለሚሸጥ መግዛት የሚፈልጉ ሁሉ በቦታው ተገኝቶ መጫረት የሚችሉ መሆኑን ፍ/ቤቱ ያስታውቋል፤ የጨረታ አሸናፋውም 1/4ኛውን ማስያዝ ይጠበቅበታል፡፡
የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ከፍ/ፍ/ቤት