በቋራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግ/ንአስ/ቡድን በወረዳው ለሚገኙ ሴ/መስሪያ ቤቶች ለ2018 የበጀት ዓመት አገልግሎት የሚውል የእስቴሽነሪ እና የመኪና መለዋወጫ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ አሸናፊ ለይቶ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ሎት 1 የመኪና ጎማ፣ ሎት 2 የመኪና መለዋወጫ ዕቃዎች፣ ሎት 3 የመናህሪያ በር ግንባታ ስለሆነም ከደረጃ 9 እና ከዚያ በላይ የሚመለከታችሁ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
- በዘመኑ የታደሰ እና በዘርፉ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
- ግዥው ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የሚፈለገውን የእቃ አይነት ዝርዝር መግለጫ ስፔስፊክሽን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ቋራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 4 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በመሂ 1 የተቆረጠ ጥሬ ገንዘብ ደረሰኝ ኮፒ አድርገው በፖስታ አሽገው ማስገባት አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን ቋራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 4 ከጥቅምት 10/2018 እስከ ጥቅምት 24/2018 ዓ/ም 12፡00 ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የመወዳደሪያ ሀሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና እና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ቋራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን በቀን ጥቅምት 25/2018 ዓ/ም 3፡30 ድረስ ማስገባት ይኖርባችኋል፡፡ በዚሁ ሰዓት ይታሽጋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቋራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 ጥቅምት 25/2018 ዓ/ም 4፡00 ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ መሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ላይ ስማቸውንና ፊርማቸው የድርጅቱ ማህተም ማስቀመጥ ይኖርባችኋል፡፡
- ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቋራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥና ንብረት አስ/ቡድን ወይም በስልክ ቁጥር 058 271 00 31 /0269 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
ማሳሰቢያ፡-
- የመክፈቻ ቀን (ሎት 1 የመኪና ጎማ ጥቅምት 25/2018 ዓ/ም 3፡30 ታሽጎ 4፡00 ይከፈታል፡፡
- ሎት 2 የመኪና መለዋወጫ እቃ ጥቅምት 25/2018 ዓ/ም 9፡30 ታሽጎ 10፡00 ይከፈታል፡፡
- ሎት 3 መናሃሪያ በር ግንባታ ህዳር 01/2018 ዓ/ም 3፡30 ታሽጎ 4፡00 ይከፈታል፡፡
- አሸናፊው ድርጅት እቃዎችን ቋራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ድረስ በማምጣት ማስረከብ አለበት፡፡
- እቃውን የምንረክበው በያዝነው የበጀት ልክ ነው፡፡
- ከላይ ደረጃ 9 ተበሎ የተለየ ለመናሃሪያ በግንባታ ብቻ የሚያገለግል ሲሆን የግንባታ ጨረው 21 ቀን በጋዜጣ ወጥቶ ይቆያል፡፡
የቋራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት