የሐራጅ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
101

በአፈ ከሳሽ የታዳጊዋ ተኩለሽ ገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ህብረት ስራ ማህበር እና በአፈጻጸም ተከሳሾች 1ኛ አቶ መሳይ በየነ እና 2ኛ አቶ ታደሰ ደስየ መካከል ስላለው የአፈጻጸም ክስ ክርክር ጉዳይ በታዳጊዋ ተኩለሽ ከተማ በአቶ ታደሰ ደስየ ስም የተመዘገበ በምዕራብ መንገድ በሰሜን አሻግሬ አድሱ፣ በደቡብ የእግር መንገድ እና በምሥራቅ ፈቃደ አሊጋዝ ተዋስኖ የሚገኝ 176.767 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ የቆርቆሮ ክዳን ቤት በጨረታ መነሻ ዋጋ ብር 256,685.97 /ሁለት መቶ ሀምሳ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ሰማኒያ አምስት ብር ከዘጠና ሰባት ሳንቲም/ ሆኖ ህዳር 05 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 እስከ 6፡00 ድረስ በግልጽ ጨረታ ስለሚሸጥ መጫረት የሚፈልግ አካል  ማንነቱን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በሰዓቱ እና በቦታዉ በመገኘት ተመዝግቦ መጫረት የሚችል መሆኑን እና የመጨረሻ አሸናፊ ያሸነፈበትን 1/4 ኛዉን ወዲያውኑ በሞደል 85 ማስያዝ የሚጠበቅበት መሆኑ ፍ/ቤቱ አዝዟል፡፡

የተኩለሽ ንዑስ ወረዳ ፍ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here