ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
30

የሰሜን ወሎ ዞን ፍላቂት ገረገራ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት የግዥና ፋይናንስ ቡድን ለሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ አቅርቦቶች ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ እቃዎች፣ ሎት 2 የጽዳት እቃዎች፣ ሎት 3 የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች፣ ሎት 4 የደንብ ልብስ፣ ሎት 5 የመኪና መለዋወጫ እቃ፣ ሎት 6 የመኪና ጎማና ባትሪ  በግልጽ ጨረታ በሎት ድምር አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾችን መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘመኑ የታደስ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የግዥ አገልግሎት መጠን ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ በላይ ከሆነ ተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዝጋቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናሉንና ኮፒ በሰም በታሸገ ፖስታ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  5. የሚገዙ እቃዎች ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ እያንዳንዱ ሎት በማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ ከገንዘብ ያዥ በመክፈል ሰነዱን መግዛት  ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) የእቃውን የአገልግሎት ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ለፍ/ገ/ከ/አስ/ገንዘብ/ጽ/ቤት ህጋዊ ደረሰኝ መሂ 1 ተቆርጦ ኮፒውን ወይም የጥቃቅን ልዩ ድጋፍ የሚያስፈልግ ጨረታ የጥቃቅን ተጠቃሚ ከሆኑ ልዩ ድጋፍ ሰነዱ ጋር ማስያዝ አለባቸው፡፡
  8. የጨረታ ሰነዱ በጋዜጣ ወጥቶ ለ15 ተከታታይ ቀናት ቆይታ  ከህዳር 01/2018 ዓ/ም እስከ ህዳር 15/2018 ዓ/ም እስከ ቀኑ 11፡30 ድረስ ሰነዱ ከፍላቂት ገረገራ ገንዘብ ጽ/ቤት/ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ግዥ ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፡፡
  9. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወጥ በሆነ በጥንቃቄ በታሸገ ፓስታ በግ/ፋ/ን/አስ/ደ/ስራ ሂደት ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን እስከ 16ኛው ቀን 3፡00 ድረስ በሳጥኑ ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ተጫራቾች በአንዱ ሎት ውስጥ የተዘረዘሩትን የእቃ አይነቶች መካከል ከፋፍሎ መጫረት አይችልም፡፡
  11. እንደ በጀት አቅም 20 በመቶ የመቀነስና የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. በእያንዳንዱ ምድብ አሸናፊ የሚሆነው ድርጅት መስፈርቱን ከጠቅላላ ድምር ዝቅተኛ ዋጋ የሞላው ነው፡፡
  13. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ባይገኙም በ16ኛው ቀን 3፡00 ተዘግቶ 3፡30 ይከፈታል፡፡
  14. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በዚሁ ስዓት ተዘግቶ በዚሁ ስዓት ይከፈታል፡፡
  15. አሸናፊ ድርጅት አሸናፊነቱ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ከ5 በሥራ ቀናት ውስጥ የውል ማስከበሪያ 10 በመቶ ለፍ/ገ/ከአስ/ገንዘብ/ጽ/ቤት በማስያዝ ውሉን መፈጸም ይኖርበታል፡፡ በተባለው ቀን ውሉን የማይፈጽም ከሆነ ያስያዘው የውል ማስከበሪያ ለመንግስት ገቢ ይሆናል፡፡
  16. አሸናፊው ውል ከፈጸመ በኋላ የአሸነፋቸውን እቃዎች በፍላቂት ገረገራ ከ/አስ/ገንዘብ/ጽ/ቤት ድረስ አጓጉዞ ያቀርባል፡፡
  17. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኝ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  18. ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 033 211 05 28 እና በ033 211 00 89 በመደወል መረጃ ማግኝት ይችላሉ፡፡

የፍላቂት ገረገራ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here