በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተ ሰላም ከተማ አስ/ከ/መ/ል/ጽ/ቤት በ2018 የበጀት አመት የ2ኛ ሩብ አመት 1ኛ ዙር የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በሚደነግገው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀጽ 8 ንዑስ አንቀፅ 1 በፊደል ተራ ሀ እስከ ሠ በተዘረዘረው መሰረት የመኖሪያና የሆቴል አገልግሎት የሚውሉ የተዘጋጁ ቦታዎችን በግልጽ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለአሸናፊዎች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ለመጫረት የሚፈልጉ ማንኛውም ግለሰብ ከህዳር 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ የቦታውን ዝርዝር መረጃ እና የጨረታ ሰነድ ለመኖሪያ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/፣ ለሆቴል ብር 400 /አራት መቶ ብር/ የማይመለስ በመክፈል እና የጨረታ ሰነድ ማስከበሪያ (ሲፒኦ) 35 በመቶ በማስያዝ በከተማ አስተዳደሩ ቅጥር ግቢ ቢሮ ቁጥር 76 ድረስ በመምጣት ዘወትር በሥራ ሰዓት ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ጊዜ ከህዳር 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ህዳር 19/2018 ዓ/ም ከቀኑ 11፡00 ብቻ ይሆናል፡፡
- ጨረታው የሚዘጋው ህዳር 19/2018 ዓ.ም ከቀኑ በ11፡00 ይሆናል፡፡
- ቦታውን መጎብኘት ለምትፈልጉ ተጫራቾች በተቋሙ ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በሚገለጸው መርሀ-ግብር መሰረት የምናስጎበኝ ይሆናል፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው ህዳር 22/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 በከተማ አስተዳደሩ ቅጥር ግቢ ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይሆናል፡፡
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ለማግኘት በስልክ ቁጥር 058 775 17 75 በመደወል ወይም ቢሮ ቁጥር 76 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
የፍኖተ ሰላም ከተማ አስ/ከ/መ/ል/ጽ/ቤት

