ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
49

በደቡብ ጎንደር አስተዳደር ዞን በሊቦ ከምከም ወረዳ የአዲስ ዘመን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሎት 1 የጽ/መሳሪያ ሎት 2 የጽዳት ዕቃዎች፣ ሎት 3 ሌሎች አላቂ ዕቃዎች (የመብራት አምፖሎች የውሃ ዕቃዎች)፣ ሎት 4 ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች (ኮፒዩተሮች)፣ ሎት 5 ሌሎች ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች (ሸልፎች ጠረጴዛዎች ካዝናዎች ወ.ዘ.ተ)፣ ሎት 6 የግንባታ እቃዎች፣ሎት7 የደንብ ልብስ ግዥ፤ ሎት 8 የህትመት አገልግሎት ግዥ አቅርቦቶችን በግልጽ ጨረታ ከአቅራቢዎች መካከል አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ መስፈርቶችን የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ተመዝጋቢ የሆኑ፡፡
  4. የገዥ መጠን ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ለሆነ ግዥዎች የተጨማሪ አሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር ከ1-4 የተዘረዘሩትንና የሚመለታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ኦርጅናል ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. የሚገዙ ዕቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ለእያንዳንዱን ሎቶች ብር 40 /አርባ ብር/ በአንድ ሰነድ ውስጥ አንድ ሰነድ ብቻ ለሚገዛ ብር 20 /ሃያ ብር/ ብቻ በመክፈል ከግ/ፋ/ንብ/አስ/ቢሮ ቁጥር 9 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) የዕቃውን (አገልግሎት) ግዥ የተጫረቱበትን ጠቅላላ ዋጋ 2 በመቶ በጥሬ ገንዘብ ደረሰኝ ኮፒውን ወይም በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ አለባቸው፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በአዲስ ዘመን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በግ/ፋ/ን/ቡ መሪ ቢሮ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሆኖ በ16 ተኛው ቀን እስከ ጠዋቱ 3:00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም በህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት (በሌሉበት) በሆስፒታሉ የመስብሰቢያ አዳራሽ ቁጥር 01 በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 03፡15 ይከፈታል፡፡
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በሌላ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ማቅረብ በህግ የተከለከለ ነው፡፡
  13. መ/ቤቱ በጨረታ ዋጋ መጠን ላይ እስከ 20 በመቶ የመቀነስና የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  14. ስለጨረታ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ግ/ፋ/ንብ/አስ/ቢሮ ድረስ በአካል በገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 141 03 71 /09 18 64 54 02 /09 18 61 70 63 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የአዲስ ዘመን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here