አውራ አምባ ማ/ፋ/ኢ/አ/ማ እነ አቶ ግዛቸው አጥናፍ የተበደሩትን ገንዘብ ባለመክፈላቸው ለብድሩ መያዣ የሆነውን ቤት በአዋጅ ቁጥር 97/90 መሠረት ታህሳስ 09/2018 ዓ.ም በግልጽ ጨረታ በሐራጅ ይሸጣል፡፡ ስለዚህ ተጫራቾች የቤቱን ይዞታ ከዚህ በታች በተጠቀሰው አድራሻ መመልከት ይችላሉ፡፡
| የተበዳሪው ስም | የንብረቱ ባለቤት | የካርታ ቁጥር | የቦታ ስፋት | አድራሻ | ቀበሌ | የጨረታው መነሻ ዋጋ | የጨረታ ቀንና ሰዓት | |
| ቀን | ሰዓት | |||||||
| እነ ግዛቸው አጥናፍ | ወ/ሮ ዙፋን ብርሃኔ | አፄቴ/11279/16 | 250 ካ.ሜ
መኖሪያ ቤት |
ባሕር ዳር ከተማ አፄ ቴዎድሮስ ክ/ከ | ልዩ ቦታ ማራኪ | 4,876,346 | ታህሳስ 09/2018 | ከ3-5
|
- ተጫራቾች በጨረታው ዕለት የጨረታ ማስከበሪያ ዋጋ የቤቱን ግምት 20 በመቶ በባንክ የተመሰከረ (ሲፒኦ) በማስያዝ መጫረት ይችላሉ፡፡
- አሸናፊ ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ አሸናፊ መሆኑ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ አጠቃሎ መክፈል አለበት፡፡
- በሐራጁ ላይ መገኘት የሚችሉት የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት፣ ተበዳሪ፣ ንብረት አስያዥ ወይም ህጋዊ ተወካዮቻቸውና የተመዘገቡ ተጫራቾች ብቻ ናቸው፡፡ ተበዳሪና ተወካዮቻቸው ባይገኙም በሌሉበት ጨረታው ይካሄዳል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ ለሆነው ተጫራች በማይክሮ ፋይናንሱ የብድር ፖሊሲ መመሪያና ቅድመ ሁኔታ መሰረት ብድር ሊመቻች ይችላል፡፡
- የተጫራቾች ምዝገባ ከጨረታው መዝጊያ ሰዓት 30 ደቂቃ በፊት ይጠናቀቃል፡፡ በጨረታው የመጨረሻ 30 ደቂቃ ውሰጥ የተጫራቾች ምዝገባ አይካሄድም፡፡
- የሐራጁ አሸናፊ ገዥ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውንም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን፣ ከስም ማዛወሪያ ጋር የተገናኙ እና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸው በህግ የተወሰኑ የግብር ግዴታዎችን ገዥው ይከፍላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታው ቀን ከመድረሱ 5 (አምስት) ቀን በፊት ከማ/ፋ ጋር በመነጋገር በስራ ሰዓት ፕሮግራም አስይዞ ለጨረታ የቀረበውን ንብረት መጎብኘት ይቻላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታው አሸናፊ ነው የሚባለው አሸናፊነቱን የሚገልጽ ደብዳቤ በጽሁፍ ሲደርሰው ነው፡፡
- ጨረታ የሚከናወነው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ቢሮ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ነው፡፡
- አጫራቹ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ 09 16 82 32 82 እና 09 18 79 00 03 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
አውራ አምባ ማ/ፋ አ/ማ

