ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

0
84

የደቡብ ጎንደር መስተዳደር ዞን የደራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት አመት በወረዳው ውስጥ ላሉ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1 ስቴሽነሪ፣ ሎት 2 የጽዳት እቃ፣ ሎት 3 ኤሌክትሮኒክስ፣ ሎት 4 ፈርኒቸር እንዲሁም ሎት 5 የግንባታ ቁሳቁስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ግዥው ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ (የቫት) ተመዝጋቢ መረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5. ጨረታው ከ1-4 ለተዘረዘሩት ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ በማድረግ ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. ተጫራቾች በድርጅታቸው ስም የተቀረፀ ማህተም ሊኖራቸው ይገባል፡፡
  7. የሚገዙ ዕቃዎችን አይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ደራ ወረዳ ገንዘብና ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 2 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
  9. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት የዕቃ አቅርቦት 2 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ በጽ/ቤቱ ደረሰኝ ገቢ በማድረግ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  10. የገዙትን የጨረታ ሰነድ ዋጋ በመሙላት እና የድርጅቱን ማህተም በማድረግ በተለያየ ፖስታ ኦርጅናሉን በማሸግ ከፖስታው ጀርባ ለደራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በማለት ስምና የሚወዳደሩበትን አይነት በመግለጽ ዘወትር በሥራ ሰዓት በጨረታ ሳጥኑ ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
  11. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን አንድ ኮፒ እና ኦርጅናልና ሥርዝ ድልዝ የሌለበት ተጫራቾችን ስም ፊርማ፣ መህተም ጨረታውን ያወጣው መ/ቤት ስምና አድራሻ በመግለጽ በደራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በተዘጋጅው የጨረታ ሳጥን ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15 ቀን ድረስ ባሉት ቀናት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  12. ጨረታ በግዥ ፋይ/ንብ/አስ ቡድን በ16ኛው ቀን የጨረታ ሳጥኑ ከረፋዱ 4፡00 ታሽጐ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም ይከፈታል፡፡
  13. ጨረታ የሚከፈትበት እለት በዓል ቀን ከሆነ የሚታሸግ እና የሚከፈተው በሚቀጥለው የሥራ ቀን ሰዓቱን ጠብቆ ይሆናል፡፡
  14. ማንኛውም ተጫራች ከነጠላም ዋጋ ሆነ ጠቅላላ ዋጋ ላይ በተጫራቾች ላይ የሚሞላ ሰነድ ላይ ሥርዝ ድልዝ ካለው ፓራፍ ቢሆንም ከውድድር ውጭ ይሆናሉ፡፡
  15. በማንኛውም ሁኔታ ተጫራቾች በሌላ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ (ተመስርቶ) መጫረት አይችልም፡፡
  16. የጨረታ መዝጊያ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የማወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግ እና ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
  17. መ/ቤቱ ጨረታዉን በሎትም ሆነ በተናጠል የማየት መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
  18. የእቃው መጠን እስከ 20 በመቶ ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል፡፡
  19. ጽ/ቤቱ በጨረታ ሰነዱ ላይ ከተዘረዘሩት ውስጥ የመረጠውን አይነት የመግዛት መብት አለው፡፡
  20. እቃው የሚቀርብበት ቦታ ደራ ወረዳ አንበሳሜ ከተማ ገንዘብ ጽ/ቤት ይሆናል፡፡
  21. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊልም የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  22. ስለ ጨረታው ዝርዝር ሁኔታ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 058 258 01 41 /09 74 08 10 74 ወይም ቢሮ ቁጥር 2 በአካል በመገኘት መጠየቅ ይችላሉ፡፡

የደራ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

 

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here