በባህርዳር እና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለይ/ዴ/ወ/ፍ/ቤ/ አገልግሎት የሚዉሉ የተለያዩ አላቂ የፅህፈት መሳሪያ እና ቋሚ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ሎት1. የጽህፈትመሳሪያ፣ ሎት2. የጽዳት ዕቃዎች፣ ሎት3. ህትመት፣ ሎት4. የህግ መፅሀፍ ፣ሎት5. ኤሌክትሮኒክስ ፣ሎት6. ቋሚ እቃዎች ፈርኒቸር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ፡ስለሆነም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ፡
- የቲን ተመዝጋቢ መሆናቸዉን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- በዘርፉ አግባብ ያለዉ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ ማስረጃ ያላቸው፡፡
- ግዥው ከ200,000 ብር /ሁለት መቶ ሽህ / በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው፡፡
- የጨረታ ሰነዱ የሚሸጥበት ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ብቻ ነዉ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ሂሳብ አንድ በመቶ በጥሬ ገንዘብ ከሆነ ከዋና ገንዘብ ያዥ በማስያዝ ለግዥ ኦፊሰሮች ማስመዝገብ ይኖርባቸዋል፡፡ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ከሆነ ከፖስታ ዉስጥ አስገብተዉ ማሸግ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ያስያዙት ገንዘብ ካለ ከአሸናፊዉ ዋጋ ጋር ተደምሮ ሲያዝ የተሸነፈዉ ተጫራች የሚያስይዘዉ ገንዘብ ይመለሳል፡፡
- ጨረታዉ የሚከፈትበት ዕለት የበዓል ቀናት ከሆነ ወደ ቀጣዩ የስራ ቀን ይሸጋገራል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ከሕዳር 22/2018 ዓ.ም እስከ ታሕሳስ 6/2018 ዓ.ም ለ15 ተከታታይ ቀናት በጋዜጣ ታትሞ የሚቆይ ሲሆን የተሞላበትን ፎርም ቲን ፤ የንግድ ፈቃድዎንና ሌሎች ያልተጠቀሱ ማስረጃዎችን በታሸገ ፖስታ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡
- ጨረታዉ የሚዘጋው ታሕሳስ 7/2018 ዓ.ም በ3፡30 ሲሆን ጨረታዉ የሚከፈተዉ ደግሞ ታሕሳስ 7/2018 ዓ.ም በ4፡00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታዉ ይከፈታል፡፡
- አሸናፊው አሸናፊነቱ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ከ5 የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ዉስጥ 10 በመቶ የዉል ማስከበሪያ በማስያዝ ዉል መያዝ አለበት፡፡
- ተጫራቾች አሽገዉ ከሚያስገቡት ሰነድ እና ፖስታ ላይ አድራሻና የድርጅቱ ማህተም መኖር አለበት፡፡
- ጫራቾች በሌላ ተጫራች ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይችሉም፡፡
- ጨረታዉን የምናወዳድረዉ በሎት ወይም በጠቅላላ ዋጋ ነዉ፡፡
- ግዥ ፈጻሚ አካል ያሸነፈውን ተጫራች በሚመርጥበት ጊዜ እንዳስፈላጊነቱ 20 በመቶ የመጨመርና የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
- የሚሞላው ዋጋ ማንኛውንም ታክስ ያካተተ መሆን አለበት፡፡
- አሸናፊዉ ያሸነፈዉን እቃ ከዋናዉ መጋዝን ይ/ዴ/ወ/ፍ/ ቤት ድረስ በማቅረብ ኦርጅናል መሆኑን በባለሞያ ታይቶ ገቢ ያደርጋል፡፡
- በጨረታዉ መሳተፍ የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች ተጨማሪ ማስረጃ ቢያስፈልጋቸዉ ለይ/ዴ/ወ/ፍ/ቤ/ በስልክ ቁጥር 09 18 25 33 03 ወይም 09 47 01 21 51 ማግኘት ይችላሉ፡
የይልማና ዴንሳ ወረዳ ፍርድ ቤት

