የደቡብ ጎንደር ዞን ገንዘብ መምሪያ ለደቡብ ጎንደር ዞን ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ ሎት 1 የጽህፈት መሳሪያ እና ሎት 2 የመኪና ጎማ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የሚያቀርቡ፡፡
- ተጫራቾች የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸውና ማስረጃዉን ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የግዥው መጠን ከብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡ የሚቀርበው ፎቶ ኮፒ የሚነበብ መሆን አለበት፡፡
- የሚገዙት የዕቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከመጫረቻ ሰነዱ ጋር ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ እትም ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ ብቻ ለእያንዳንዱ ሎት በመክፈል ቢሮ ቁጥር 12 ከረዳት ገንዘብ ያዥ መግዛት /ማግኘት/ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደርበት ለሎት አንድ 30,000 /ሰላሳ ሽህ ብር/ ለሎት ሁለት 60,000 /ስልሳ ሽህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡ በጥሬ ገንዘብ ከሆነ በመሂ 1 በመቁረጥ ደረሰኙን አብረው አሽገው ማስገባት ይኖርበታል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወጥ ወይም አንድ ወጥ በሆነ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በገንዘብ መምሪያ በግዥ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 14 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ 15ኛው ቀን ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በገንዘብ መምሪያ በግዥ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 14 በ16ኛው ቀን በ3፡00 ታሽጎ 3፡30 ይከፈታል፡፡ የጨረታ መክፈቻ ቀኑ ቅዳሜ፣ እሁድ እና የህዝብ የበዓል ቀን ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ ቢኖሩም ባይኖሩም ጨረታውን ከመክፈት አያግድም፡፡
- ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን እቃዎች ከግዥ ፈፃሚ መስሪያ ቤት ንብረት ክፍል ድረስ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- አሸናፊው የሚለየው በጠቅላላ ድምር ነው፡፡
- አሸናፊው ድርጅት ባሸነፈበት የዋጋ ድምር 10 በመቶ የውል ማስከበሪያ ማስያዝ አለበት፡፡
- አሸናፊው አሸናፊነቱ እንደተገለፀለት ከ5 ተከታታይ የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ መጥቶ ውል መውሰድ አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ስለጨረታው ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 14 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 441 07 53 በመደወል ማብራሪያ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የደቡብ ጎንደር ዞን ገንዘብ መምሪያ

